መነሻ ገጽ ወላይታ ድቻ የወላይታ ድቻ ተጫዋቾች ቅሬታቸውን አሰምተዋል
ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የወላይታ ድቻ ተጫዋቾች ቅሬታቸውን አሰምተዋል

አጋራ
አጋራ

 

የወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾች በኮሮና ቫይረስ ውድድሮች ከተቋረጡ ጀምሮ የሶስት ወር ደሞዛቸው ባለመከፈሉ ምክንያት ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

በሀገራችን ኮሮና ቫይረስ ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ የስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ከታገዱ ወራቶች ሲቆጠሩ በዚህም የተለያዩ ክለቦች ለተጫዋቾቻቸው ደሞዝ ባለመክፈል ቅሬታ ይነሳል። የዚህ ችግር ሰለባ የሆኑት የወላይታ ድቻ ተጫዋቾች ከ3ወር በላይ ደሞዝ እንዳልተከፈላቸው የክለቡ ተጫዋቾች በተለይ ለሀትሪክ ስፖርት በስልክ ቅሬታቸውን አሰምተዋል። “ከሶስት ወር በላይ ደሞዝ አልተከፈለንም በዚህም ከፍተኛ ችግር ውስጥ ገብተናል በተደጋጋሚ የሚመለከተውን አካል አነጋግረን ዛሬ ነገ ከ ከማለትውጪ ምንም ለጥያቄያ ምላሽ ሳይሰጡን ወራት ተቆጥረዋል በተጨማሪም ክለቡ ግዜያችን በምን መልኩም እያሳለፍን እንደሆነ በቅርበት አለመጠየቁ ይበልጥ ነገሩ አስከፊ አድርጎብናል ያሉት ተጫዋቾቹ እኛ የቤተሰብ አስተዳዳሪዎች ነን መተዳደሪያችንም እግር ኳሱ ስለሆነ ክለቡ ምላሽ የማይሰጠን ከሆነ ጉዳዩን ወደ ህግ እንወስደዋለንም ብለዋል”። ሲሉ የክለቡ ተጫዋቾች ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

ጉዳዩን ለማጣራት ባደረግነው ጥረት በተደጋጋሚ ወደ ክለቡ አመራሮች ስልክ ብንደውልም ስልክ ባለማንሳታቸው ምክንያት የነሱን ምላሽ ሳናካትት ቀርተናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

ገረሱ ሸመና መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቀለ

በሊጉ ለመቆየት እየዳዱ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታዎች ረዳት አሰልጣኝ ሾመዋል። በኢትዮጵያ እግር...

ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...