የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በ2011 ዓ.ም ሲያካሄዳቸው በነበሩት የተለያዩ 6 ሊጐች ላይ ውድድሩን በስኬት ላጠናቀቁት እግር ኳስ ተጫዋቾችና የተለያዩ የእግር ኳስ ባለሙያዎች ለኮከብ ሽልማት በዕጩነት በመመልመልና በመለየት ቅዳሜ ህዳር 27 ቀን 2012 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል ከምሽቱ 12፡00 የኮከቦች ሽልማት ሥነ-ሥርዓት አዘጋጅቷል፡፡ የሽልማቶቹ ዘርፍ ኮከብ አሠልጣኝ፣ ኮከብ ተጫዋች ፣ ኮከብ ግብ አግቢ፣ ኮከብ ግብ ጠባቂ እንዲሁም ምስጉን ዋና ዳኛ እና ምስጉን ረዳት ዳኛ ሲሆኑ በተጨማሪም የሕይወት ዘመን ተሸላሚ እና ልዩ ተሸላሚዎችን ያካተተ ነው፡፡ በዕጩነት የተመረጡት ኮከብ ተጫዋቾች ዝርዝር የሚከተሉትን ይመስላል፡፡
ከአንደኛ ሊግ
ተጫዋቶች
1. ፈቱ አብደላ ከኮልፌ ቀራንዮ ክ/ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
2. በላይ ገዛኸኝ ከባቱ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
ግብ ጠባቂዎች
1. ቴዎድሮስ ከለሎ ከኮልፌ ቀራንዮ ክ/ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
2. ወንደሰን ረጋሳ ከባቱ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
ከከፍተኛ ሊግ
ተጫዋቶች
1. ጌቱ ኃ/ማርያም ከሰበታ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
2. አህመድ መሀመድ ከወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
3. ሱራፌል ጌታቸው ከሀዲያ ሆሳዕና እግር ኳስ ክለብ
ግብ ጠባቂዎች
1. አሰግድ አክሊሉ ከሰበታ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
2. ጆርጅ ደስታ ከኢትዮጵያ መድን እግር ኳስ ክለብ
3. አንተነህ ሀብቴ ከገጣፎ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
ከወንዶች ኘሪሚየር ሊግ
ተጫዋቾች
1. ሱራፌል ዳኛቸው ከፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ
2. ሃብታሙ ገዛኸኝ ከሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ
3. አማኑኤል ገ/ሚካኤል ከመቐሌ 70 እንደርታ እግር ኳስ ክለብ
ግብ ጠባቂዎች
1. ፍሊኘ አቫኖ ከመቐሌ 70 እንደርታ እግር ኳስ ክለብ
2. ስማኪ ሚካኤል ከፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ
3. መሳይ አያኖ ከሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ
ከሴቶች ኘሪሚየር ሊግ 1 ዲቪዚዮን
ተጫዋቾች
1. ሰናይት ቦጋለ ከአዳማ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
2. ሴናፍ ዋቁማ ከአዳማ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
3. ምርቃት ዘለቀ ከሐዋሳ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
ግብ ጠባቂዎች
1. ማርታ በቀለ ከመከላከያ እግር ኳስ ክለብ
2. ንግስት መአዛ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እግር ኳስ ክለብ
3. እምወድሽ ይርጋሸዋ ከአዳማ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
ከሴቶች ኘሪሚየር ሊግ 2 ዲቪዚዮን
ተጫዋቾች
1. ዮርዳኖስ በርሄ ከመቐሌ 70 እንደርታ
2. ንግስቲ ሀይሉ ከአቃቂ ክ/ከተማ እግር ኳስ ክለብ
3. ቤተልሔም አምሳሉ ከፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ
ግብ ጠባቂዎች
1. አዲስ የአብርሃም ከአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ እግር ኳስ ክለብ
2. አይናለም ሽታ ከቂርቆስ ክ/ከተማ እግር ኳስ ክለብ
3. ጺዮን ተፈራ ከሻሸመኔ ከተማ እግር ኳስ ክለብ
አስተያየት ይስጡ