የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የከፍተኛ ሊግ ኮሚቴ በከፍተኛ ሊጉ የሚሳተፉ ክለቦች የተጫዋች ምዝገባ በ 08/03/2012 ዓ/ም የተጠናቀቀ ቢሆንም ከክለቦች በቀረበ ጥያቄ የምዝገባውን ጊዜ እሰከ 17/03/2012 ዓ/ም ያራዘመ ሲሆን በተባለው ጊዜ ምዝገባቸውን የማያከናውኑ ክለቦች ከተጠቀሰው ጊዜ በኋላ የእንመዝገብ ጥያቄ ቢያቀርቡ ተቀባይነት እንደማይኖረው ኮሚቴው አሳስቧል ፡፡
በከፍተኛ ሊግ ክለቦች መካከል የሚኖረው ውድድር ዕጣ የማውጣት ስነስርዓት ህዳር 24/2012 ዓ/ም የሚከናወን ሲሆን በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የከፍተኛ ሊግ በ 36 (ሰላሳ ስድስት) ክለቦች መካከል በሶስት ምድብ በመከፈል ውድድራቸውን በ27/03/2012 ዓ/ም ይጀምራሉ፡፡
አስተያየት ይስጡ