መነሻ ገጽ ካፍ የኢ.እ.ፌ ፕሬዝዳንት ለሰዓታት ቦሌ አየር ማረፊያ ከቆዩት የካፍ ፕሬዝዳንት ጋር ተወያዩ
ካፍዜናዎች

የኢ.እ.ፌ ፕሬዝዳንት ለሰዓታት ቦሌ አየር ማረፊያ ከቆዩት የካፍ ፕሬዝዳንት ጋር ተወያዩ

አጋራ
አጋራ

የካፍ ፕሬዝዳንት አህመድ አህመድ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ማምሻውን በአዲስ አበባ ተወያዩ።
ወደ ካይሮ ለማቅናት ዛሬ ነሐሴ 30/2012ዓ.ም ከቀኑ 9፡49 ከማዳጋስካር በኢትዮጵያ አየር መንገድ የተጓዙት የካፍ ፕሬዚዳንት ማምሻውን ቦሌ አለማቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የኢ.እ.ፌ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ኢሳያስ ጅራ እና የጽ/ቤት ኃላፊው አቶ ባህሩ ጥላሁን አቀባበል አድርገውላቸዋል። የካፍ ፕሬዝዳንት አህመድ አህመድ በቦሌ አየር ማረፊያ የVIP Salone ለሰዓታት የቆዩ ሲሆን በቆይታቸው ከአቶ ኢሳያስ ጅራ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።


ካፍ በታህሳስ ወር አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስ አበባ ለማድረግ ስለወሰነ መደረግ ስለሚገባቸው ቅድመ ዝግጅቶች ላይ ውይይት አድረገዋል።
በቀጣይ የሚደረጉ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ውድድሮች እና ኮቪድ 19 በአፍሪካ ላይ እያሳደረ ስላለው ተጽኖ እንዲሁም ኢትዮጵያ ውድድሮችን ለማስጀመር እያደረገች ስላለው ጥረት ተወያይተዋል።
ማምሻውንም ወደ ግብጽ ካይሮ ያቀኑ ሲሆን ሴፕቴምበር 10 የካፍ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በቪዲዮ በመታገዝ ስብሰባ በማካሄድ የተለያዩ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል።

Via-EFF

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...