መነሻ ገጽ ዜናዎች የኢት.እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከመስከረም 1/2013 ጀምሮ አቶ መኮንን ኩሩ የሚባል ዳይሬክተር የለኝም አለ
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የኢት.እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከመስከረም 1/2013 ጀምሮ አቶ መኮንን ኩሩ የሚባል ዳይሬክተር የለኝም አለ

አጋራ
አጋራ

 

..ቦታውን አቶ ሰለሞን ገ/ስላሴ በጊዜያዊነት ይዘውታል

ከውስጥም ከውጪም በመጣብኝ ጫና ስራዬን ለቀኩ… ሲላቸው ቦታዬ ላይ ነኝ ..ሲያሻቸው ደግሞ ፈቅጄ ቦታውን ለቅቄያለሁ ሲሉ የነበሩትና ቢያንስ ባለፉት 10 አመታት ቦታው ላይ ይኑሩም አይኑሩም ተቃውሞ ሲቀርብባቸው የነበሩት የፌዴሬሽኑ የቴክኒክ ዳይሬክተር አቶ መኮንን ኩሩ ያቀረቡትን የስራ መልቀቅ ጥያቄ ተቀባይነት በማግኘቱ ከሃላፊነታቸው ተነስተዋል፡፡

አቶ መኮንን ባቀረቡት የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ “…..ከውጭ ባለብኝ ጫና የሚፈለገውን ያህል ልሰራ ስላልቻልኩ……”ከሚል ሃረግ ጋር ቦታውን እንደማይፈልጉት
በመግለጽ ሰው እስኪገኝ ድረስ ስራውን እየሰሩ እንደሚቆዩ ገልጸው የኢንስትራክተርነት ስራቸውን እንደሚሰሩ በማረጋገጥ ፌዴሬሽኑን በሙያቸው ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አባላት እጃቸው ላይ ያለውን ስራ እስኪጨርሱ ድረስ እንዲቆዩ ይደረግ በሚልና አይ አልፈልግም ካለ ውጤታማ ስለማይሆን ይሰናበት በሚሉ ሁለት ሃሳቦች ላይ ከተወያዩ በኋላ የለቁኝን ጥያቄ ተቀብለውታል፡፡

አመራሮቹ ከዚህም በላይ የፌዴሬሽኑ ምክትል ጸሃፊ አቶ ሰለሞን ገ/ስላሴ በጊዜያዊነት ሃላፊነቱን ደርበው እንዲሰሩ መወሰናቸው ታውቋል

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...