መነሻ ገጽ ዜናዎች የኢትዮጵያ 1ኛ ሊግ የ2010 ግምገማ እና የ2011 የእጣ ማውጣት ስነስርአት ተካሂዷል
ዜናዎችየኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ

የኢትዮጵያ 1ኛ ሊግ የ2010 ግምገማ እና የ2011 የእጣ ማውጣት ስነስርአት ተካሂዷል

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ 1ኛ ሊግ የ2010 ግምገማ እና የ2011 የምድብ ድልድል እና የእጣ ማውጣት ስነስርአት በዛሬው እለት በኢትዮጵያ ሆቴል ተካሂዷል።
በ2010 የ1ኛ ሊግ ውድድር በርካታ ችግሮች ቢገጥሙንም ውድድሩን መፈፀም ችለናል ሲሉ የፌዴሬሽኑ አካላት ገልፀዋል።
በሳለፈነው የ1ኛ ሊግ ውድድር 57 ክለቦች ሲካፈሉ 486 ጨዋታዎችን አከናውነዋል።

በ2010 ውድድር ዓመት ከነበሩ ችግሮች ውስጥ :-

¤ በጨዋታ ላይ ዳኞች በደጋፊዎቹ እና በክለብ አባለት መደብደብ
¤ በውድድሩ ከክለቦች የቦታ እርቀት የተነሳ ዳኞችን በበቂ ሁኔታ ለመመደብ መቸገር።
¤ በጨዋታ ሜዳዎች ላይ በቂ የፀጥታ ሀይል አለመኖር።
¤ የዳኞችን የጨዋታ አፈፃፀም በተመለከተ ኮሚሽነሮች የተሟላ ሪፖሪት አለማቅረብ።
¤ በውድድሩ ሜዳዎች ደጋፊ እና ተጫዋቾችን እሚለይ አጥር (ሽቦ) አለመኖሩ።
¤ በአንዳንድ የውድድር ቦታ ሜዳዎች ለውድድር አመቺ ያለሁን ሜዳዎች መኖሩ።

በውድድሩ ለነበሩ ችግሩች የተሰጡ መፍትሔዎች :-
¤ በውድድሩ ወቅት የዳኞች ስም እየተጠቀሱ እንዳይመደቡ እሚጠየቁ ጥያቄዎችን ያለመቀበል።
¤ የጨዋታዎቹ ክብደት እየታየ ሲኒየር ዳኞችን መመደብ።
¤ ከጨዋታ ታዛቢዎች በተጨማሪ በየጨዋታው የኮሚቴ አባላትን በታዛቢነት እንዲገኙ ማድረግን::
¤ በየውድድሩች ላይ ከፀጥታ አካላት ጋር በመነጋገር ችግሮች ሳይፈጠሩ መፍትሔ እንዲወሰድ ማድረግ።

በመጨረሻም 63 ክለቦች በ6 ምድብ እሚሳተፉ ክለቦች ምድቦቻቸውን ይፋ ሆኗል።

የ2011 የኢትዮጵያ 1ኛ ሊግ ክለቦች የጨዋታ መርሐ ግብራቸውን በቀጣይ ቀናት በድህረ-ገፃችን ላይ እምናሳውቅ መሆናችንን እንገልፃለን።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...