መነሻ ገጽ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዳሜ ይጀመራል
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዳሜ ይጀመራል

አጋራ
አጋራ

2012 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የፊታችን ቅዳሜ በይፋ እንደሚጀመር
የ2ዐ12 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር
አዘጋጅ አብይ ኮሚቴ አስታውቋል፡፡ በወጣው
የዕጣ አወጣጥ መሠረት የሊጉ የመጀመሪያ
ሳምንት ጨዋታዎች ቅዳሜ ሲጀምር በአዲስ
አበባ ስታዲየም ሰበታ ከተማ ወልዋሎ
አዲግራትን ያስተናግዳል፡፡ የሰበታ ከተማ
ስታዲየም ለውድድሩ የሚጠበቅበትን መመዘኛ
አላሟላም በሚል በመታገዱ የሜዳ ላይ
ጨዋታዎችን በሙሉ በአዲስ አበባ ስታዲየም
እንዲያካሄድ ተወስኗል፡፡ ይህም አዲስ ከቅዱስ
ጊዮርጊስና ከኢትዮጵያ ቡና በመቀጠል አበባ
ስታዲየምን እንደሜዳው ለመጠቀም እድል
ያገኘ ሶስተኛው ክለብ ሆኗል፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከወልቂጤ ከተማ
ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በሀድያ ሆሳዕና
ወይም በዝዋይ ስታዲየም መሆኑ ታውቋል፡፡
የወልቂጤ ስታዲየም እንደሰበታው ስታዲየም
ለውድድር ዝግጁ አይደለም ተብሎ ታግዷል፡
፡ የሽረ ስታዲየም መመዘኛ ባለማሟላት
በመታገዱ ስሁል ሽረ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር
በሚያደርገው ጨዋታ መቐለ ላይ የሚካሄድ
መሆኑ ታውቋል፡፡ አዳማ ላይ አዳማ ከተማ
ፋሲል ከነማን፣ ጅማ ላይ ጅማ አባጅፋር
ባህርዳር ከተማን፣ መቐለ ላይ መቐለ 7ዐ
እንደርታ ሀድያ ሆሳዕናን እንዲሁም ሀዋሳ ላይ
ሀዋሳ ከተማ ድሬደዋ ከተማን ያስተናግዳሉ
ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የመጀመሪያው ሳምንት
ትልቁ ጨዋታ በደቡብ ደርቢ ወልይታ ድቻ
ሲዳማ ቡናን የሚያስተናግድበት ጨዋታ ነው፡
፡ የአምናው የደርሶ መልስ ጨዋታ ከፀጥታ
ስጋት የተነሣ አዲስ አበባ ላይ የተካሄደ ሲሆን
የአዲሱ የሊግ ኮሚቴ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፍቃደ
ማሞ ግን ይህ እንደማይደገም ተናግረዋል፡፡
“የአምናው ታሪክ በፍፁም አይደገምም ሕጉን
ተግባራዊ ለማድረግ እንደፍራለን ጨዋታው
እዚያው ወላይታ ላይ ይደረጋል” ሲሉ
መናገራቸው ይታወሳል፡፡ ነገር ግን የጨዋታው
ቦታ ማተሚያ ቤት እስከገባነበት ድረስ ይፋ
አልተደረገም፡፡ ምናልባት ዛሬ ሊግ ኮሚቴው
በሚያደርገው ስብሰባ ውሳኔው ይታወቃል
ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ከተጨዋቾች እና አሰልጣኞች የደሞዝ
ክፍያ ጋር በተያያዘ ውዝግብ ውስጥ ያሉት
ጅማ አባጅፋርና ወልዋሎ አዲግራት
የሚጠበቅባቸውን ክፍያ ባለመክፈላቸው
የፕሪሚየር ሊጉ የመጀመሪያ ሳምንት
ጨዋታዎች ያመልጣቸው ይሆን? የሚለው
ጥያቄ እስካሁን ድረስ ምላሽ አላገኘም፡፡ ደሞዝ
የተከለከሉት ተጨዋቾችስ ለቡድኖቻቸው
ይሰለፉ ይሆን? የሚለው አጓጊ ሆኗል፡፡ በጉዳዩ
ዙሪያ የወልዋሎ አዲግራት አመራሮች ክፍያውን
የምንፈፅምበትን ቁርጥ ያለ ቀን አሳውቁን
ብለው በማሳወቃችን የመታገድ ስጋት የለብንም
ሲሉ የጅማ አባጅፋር ኃላፊዎችም የሶስት ወር
ደመወዝ ከፍለናል ያለውን ቀሪ ክፍያ በጊዜ
ገደብ ስለምንከፍል እገዳ ይኖርብናል ብለን
አንሰጋም ሲሉ የክለቦቻቸውን አቋም ለሀትሪክ
ገልፀዋል፡፡ አጠቃላይ ሁኔታውን ለማረጋገጥ
ወደ ዲሲፒሊን ኮሚቴ ዋና ፀሐፊ አቶ አብራር
ተንቀሳቃሽ ስልክ ብንደውልም ምላሽ ማግኘት
አለመቻላችንን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...