በህንድ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ዓለም ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታ የመጀመሪያ ጨዋታውን ሽንፈት የገጠመው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ሽንፈቱን ሽንፈቱን በመቀልበስ ወደቀጣዩ ዙር ለማለፍ ይጠቅሙኛል ያላቸውን አረጋሽ ካልሳ ገነት ኃየሉ እና የንግድ ባንኳ ሁለተኛ ግብ ጠባቂ ምህረት ተሰማን ወደ ቡድኑ በመቀላቀል ልምምዳቸውን አከናውነዋል።
የኢትዮጵያ የሴቶች ከ17 ዓመት በታች ቤሔራዊ ቡድን እሁድ በ10፡00 ሰዓት በባህርዳር ኢንተርናሽናል ስታዲየም ከኡጋንዳ አቻው ጋር ሁለተኛውን ጨዋታ የሚያከናውን ይሆናል።
አስተያየት ይስጡ