ቅዳሜ ታህሳስ 6 በትግራይ ስታድየም እንዲካሄድ መርሃ ግብር የወጥለት የወልዋሎና ድሬዳዋ ጨዋታ በተያዘለት ፕሮግራም እንደሚካሄድ ታውቋል።
በ5ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከተያዘለት መርሃ ግብር ኣንድ ቀን ዘግይተው እንዲጫወቱ የተገደዱት ወልዋሎዎች ለነገው ጨዋታ ማዘጋጅያ በቂ ጊዜ እንድናገኝ ጨዋታው አንድ ቀን ይራዘምልን የሚል ደብዳቤ ለፌዴሬሽኑ ቢያስገቡም ጥያቄያቸው ተቀባይነትን ሳይገኝ ቀርቷል።
በጥሩ ወቅታዊ ብቃት የሚገኙት ሁለቱም ክለቦች ጨዋታቸውን ነገ 9 ሰዓት በትግራይ ስታድየም ሚያካሂዱ ይሆናል።
አስተያየት ይስጡ