መነሻ ገጽ ዋልያዎቹ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከዋሊያ ቢራ ጋር የስፖነሰር ሺፕ ስምምነት ተፈራረመ
ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከዋሊያ ቢራ ጋር የስፖነሰር ሺፕ ስምምነት ተፈራረመ

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከዋሊያ ቢራ አክሲዮን ማህበር ጋር የብቸኛ የስፖንሰር ሺፕ ስምምነት ዛሬ መጋቢት 11/2011ዓ.ም በካፒታል ሆቴል ተፈራረመ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ላለፉት አራት ዓመታት 56ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ አጋርነቱን በተግባር ያረጋገጠው ዋሊያ ቢራ አክሲዮን ማህበር መሆኑ ይታወቃል፡፡

በመሆኑም ዋሊያዎቹ ሲነሱ ዋሊያ ቢራ፤ ዋሊያ ቢራ ሲነሳ ዋሊያዎቹ ይታወሳሉ፡፡
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና ዋሊያ ቢራ አክሲዮን ማህበር ለቀጣዮቹ አራት አመታት የሀምሳ ስድሰት ሚሊዮን ብር ብቸኛ የስፖንሰር ሺፕ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ይህ አዲስ ስምምነት የኢትዮጵያ የወንድ እና የሴት ዋና ብሔራዊ ቡድኖችን ላይ የተደረገ ስምምነት ነው፡፡ በተጨመሪም ከዚህ በፊት ከነበረው ስምምነት በተለየ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከቢራ እና ማልት መጠጦች ውጪ ከሌሎች የመጠጥ ተቋማት ጋር የስፖነሰር ሺፕ ስምምነት እንዲፈራረም ስምምነቱ ይፈቅድለታል፡፡

በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ”የእኛ እና የዋሊያ ቢራ አክሲዮን ማህበር የብቸኛ ስፖንሰር ሺፕ ስምምነት በዋናነት የምግብና መጠጥን አስመልክቶ የወጣውን አዋጅ መሰረት አድርጎ ለመስራት እና በተመሳሳይ ማግኘት የሚገባውን ጥቅም ለማስጠበቅ ግዴታ እና መብትን በግልጽ የሚያሳይ እንዲሆን ተደርጎ የተሰራ ስምምነት ነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ይህ ስምምነት ከ2019 እስከ 2022 እ.ኤ.አ ለተከታታይ 4ዓመታት የሚቆይ ሲሆን የስፖንሰር ሺፑ ስምምነቱም 56ሚሊዮን ብር ነው፡፡

Source – eff

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...