መነሻ ገጽ መቐለ 70 እንደርታ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መቐለ 70 እንደርታ ላይ የቅጣት ውሳኔ እስተላለፈ
መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መቐለ 70 እንደርታ ላይ የቅጣት ውሳኔ እስተላለፈ

አጋራ
አጋራ

 

ሚያዝያ 26 ትግራይ ስታድየም ላይ በተካሄደው የደደቢት እና ፋሲል ጨዋታ ላይ በታየው የስፖርታዊ ጨዋነት ጉድለት ምክንያት ከዚህ በፊት ደደቢት ላይ ተወስኖ የነበረው የቅጣት ውሳኔ የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ውሳኔው ሙሉ በሙሉ በመቀልበስ መቐለ 70 እንደርታ ላይ ኣንድ ጨዋታ በዝግ ስታድየም እንዲጫወት፣የ75 ሺህ ብር እንዲከፍል እንዲሁም 5 የተጎዱትን የፋሲል ተጨዋቾች የህክምና ወጪ እንዲሸፍን ተወስኖበታል።

የዲስፒሊን ኮሚቴው ከዚህ ቀደም ደደቢት ላይ ሁለት ጨዋታዎች በዝግ ስታድየም እንዲያካሂድ እንዲሁም የ150 ሺህ ብር ቅጣት እስተላልፎ የነበረ ቢሆንም ደደቢትና ፋሲል ባቀረቡት የይግባኝ ጥያቄ መሰረት ጉዳዩን ሲመለከተው የነበረው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ቅጣቱን ሙሉ በሙሉ ከደደቢት በመሻር መቐለ 70 እንደርታ ላይ ወስኗል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...