የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን 19 ሳምንት የኢትዮጵያ ፕርምየር ሊግ መርሀግብር በነበረው በወልዲያ እና ፋሲል ከነማ ጨዋታ ዙርያ የሚከተለውን ውሳኔ ወስኗል።
1. የወልዲያ እግርኳስ ክለብ ከፋሲል ከተማ እግርኳስ ክለብ ጋር 03/08/2010.ዓ.ም ያደረገው ጨዋታ በፎርፌ ተሸናፊ ሆኖ ለፋሲል ከተማ እግርኳስ ቡድን 3ነጥብ እና 3ጎል እንዲመዘገብለት ተወስኗል፡፡
2. በወልዲያ ሼክ አሊ አላሙዲ ስታድየም ጥፋት ከፈፀሙበት ከሚያዝያ 02/08/2010 ዓ.ም አስከ ሚያዚያ 02/08/2011 ዓ.ም ድረስ ጨዋታዎች የመጫወት መብት እንዲያጡ እና በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የሚካሄዱ ማንኛውም ውድድሮች እንዳይካሄዱ ተወስኗል፡፡
3. ክለቡ የሚያደርጋቸውን የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እግርኳስ ውድድሮች ከከተማው 500ኪ.ሜ በላይ በሚገኝው ሜዳ ላይ ውድድሩን እንዲያካሂድ ተወስኗል፡፡
4. የክለቡ ደጋፊዎች በፈፀሙት ሁከት፣ እረብሻ እና ጥፋት 250,000 ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲከፉሉ ተወስኗል፡፡
5. ክለቡ በዳኞች ላይ በደረሰው ጉዳት በሚገኝበት ሆስፒታል እንዲያሳክም እና ወደፊት በሚቀርበው ማስረጃ መሰረት ክለቡ ለኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ድረስ ቀርቦ እንዲከፍል ተወስኗል፡፡
6. ክለቡ ደጋፊዎቻቸውን ስለ ስፖርታዊ ጨዋነት እስከ ሚያዚያ 02/08/2011 ዓ.ም ድረስ በጥልቀት እንዲያስተምሩ፡፡ ይህንን ካልፈፀሙ የወልዲያ እግርኳስ ክለብ ከውድድሩ እንዲታገድ ተወስኗል፡፡
7.አሰልጣኝ ዘማርያም ወ/ጊዮርጊስ የጨዋታወን ዳኛ በማነቅ፣ በመሳደብ እንዲሁም ተጫዋቾችን እና ደጋፊዎችን ለረብሻ እንዲነሳሱ በማድረግ 1ዓመት ከማንኛውም እግርኳስ አሰልጣኝነት እንዲታገዱ እና ብር 25,000 ቅጣት እንዲከፍሉ ተወስኗል፡፡
8.ተጫዋች ብሩክ ቃልቦሬ ዳኛ ለመማታት ሙከራ በማድረጉ እና ተጫዋቾችን እንዲሁም ደጋፊዎችን ለረብሻ በማነሳሳት 1 ዓመት ከማንኛውም እግር ኳስ ተጫዋችነት እንዲታገድ እና ብር 10,000 የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍል ተወስኗል፡፡

አስተያየት ይስጡ