መነሻ ገጽ ሰበር ዜና የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ኢያሱ መርሃ ጽድቅ ከቦታቸው እንዲነሱ ተወሰነ
ሰበር ዜናዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ኢያሱ መርሃ ጽድቅ ከቦታቸው እንዲነሱ ተወሰነ

አጋራ
አጋራ

 

ላለፉት ጥቂት ወራቶች የፌዴሬሽኑን የጽ/ቤት ስራ ሲመሩ የነበሩት ዶ/ር ኢያሱ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ዛሬ ባደረገው ስብሰባ ሃላፊነታቸውን በብቃት አልተወጡም የጽ/ቤቱ
አስተዳደራዊ ስራን አልመሩም በሚል ውሳኔውን ሰጥቷል፡፡
ከፌዴሬሽኑ ውስጥ አዋቂ በተገኘ መረጃ ዶ/ሩ በቅርብ ጊዜያቶች እየወሰኑ ያለው ውሳኔ ቅሬታ እያስነሳ ሲሆን የዲሲፕሊንና የይግባኘ ሰሚ ኮሚቴ ውሳኔ ላይ ጣልቃ በመግባት እንዲሁም ተፈጻሚ ባለማድረግ የክለቦች ቅጣት ላይ ተግባራዊ እንዳይደረግ በማዘዝ ደመወዝ ለመክፈል ወራቶች እንዲጨመርላቸው በማድረግ በኮሚቴዎች ስራ ላይ ጣልቃ ገብተዋል በሚል ቅሬታ ሲሰማባቸው ቆይተዋል፡፡ በሳምንታት በፊት አሠልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ በዲሲፕሊን ኮሚቴ ሲቀጣ ይግባኝ በመጠየቅ እስከዛው ድረስ የዲሲፕሊን ኮሚቴ ውሳኔ እንዲታገድ ቢጠይቅም በህግ የተሠጠውን መብት ወደጎን በማለት ሃላፊነታቸውን አልተወጡም በሚል ቅሬታ ቀርቦባቸዋል፡፡ ስራ አሰፈጻሚዎቹም በዚህና ሌሎች አስተዳደራዊ ክፍተቶች ጫና ውስጥ ሳይገቡ እንዳልቀሩ ተገምቷል፡፡
ቦታው እንደ እሳት የሚፋጀው ይሄ ቦታን በሚገባ ለመምራት ጠንካራ አመራርና ውሳኔ ሰጪነት የሚጠበቅ ቢሆንም የአለማያ ዩኒቨርስቲ ምሩቁ ግን ሳይከብዳቸው እንዳልቀረ ይገመታል፡፡ የስራ አስፈጻሚው ውሳኔ ከነገ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡ ስለመረጃውወደ ዋና ፀሃፊው ጋር ብደውልም ስልካቸውን ሊያነሱ አልቻሉም፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...