መነሻ ገጽ ዜናዎች የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ክለቦች የእጣ ማውጣት ስነስርዓት ተከናወነ፡፡
ዜናዎችየኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ

የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ክለቦች የእጣ ማውጣት ስነስርዓት ተከናወነ፡፡

አጋራ
አጋራ

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ክለቦች የ2011 ዓ.ም የውድድር አፈፃፀም ውይይትና የ2012 ዓ.ም ውድድር እጣ ማውጣት ስነ ስርዓት ዛሬ በ 18/03/2012 ዓ.ም በራስ ሆቴል ተካሂዷል፡፡
በዚህ ኘሮግራም ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል አቶ ዘሪሁን ቀቀቦ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም ስፖርታዊ ጨዋነት ቅድሚያ እንዲሰጠው በአፀንኦት ተናግረዋል፡፡


ስፖርት በተለይም እግር ኳስ የአለማችን ትልቁ የደስታ ምንጭ ነው፡፡ ህብረተሰብን በማስተሳሰር በአንድነትና በወንድማማችነት የሚያቅፍ ትልቅ ምሰሶ ነው፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ይህ የሚወደድና የሚከበር እግር ኳስ በሃገራችን በስፖርታዊ ጨዋነት መጓደል ምክንያት ከማቀራረብ ይልቅ እያራረቀ ከመወደድ ይልቅ የስጋት ምንጭ እየሆነ ክብሩም እየቀነሰ ነው፡፡ ይህም በመሆኑ የኢትዩጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዚህ አመት ለስፖርታዊ ጨዋነት ከፍ ያለ ትኩረት ይሰጣል፡፡
ክለቦችም ይህንን በመገንዘብ ከውጤት ባልተናነሰ ለስፖርታዊ ጨዋነት ትኩረት ልትሰጡ ይገባል፡፡
በእናንተ ጨዋታ ህብረተበቡ መደሰት እንጂ ማዘን የለበትም የስፖርታዊ ጨዋነትን ጉዳይ ከፍ ያለ ትኩረትና ቦታ እንድትሰጡት በፌዴሬሽኑ ስም አደራ ብለዋል፡፡
በመቀጠልም የ2012 ዓ.ም የኢትዮጵያ 1ኛ ሊግ ተሳታፊ ክለቦች በተገኙበት የ 2011 ዓ.ም የውድድር ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ተህሳስ 5/2012 ዓ.ም የሚጀመረው የ2012 ዓ.ም የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ክለቦች የውድድር መርሃ ግብር በስድስት ምድብ በመከፈል እጣ የማውጣት ስነስርዓት ተኳሂዷል፡፡

via – EFF

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...