By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ተጨዋች ሰይፈ ውብሸት /ፕሮም/ ለኮሮና ቫይረስ ከፍተኛ እርዳታ አደረገ
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ተጨዋች ሰይፈ ውብሸት /ፕሮም/ ለኮሮና ቫይረስ ከፍተኛ እርዳታ አደረገ

መሸሻ ወልዴ
መሸሻ ወልዴ 6 years ago
Share
SHARE

የእግር ኳስ ተጨዋችነት ዘመኑን በክለብ ደረጃ ላሳደገው ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና በኋላም ላይ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ለጥቂት ጊዜያት ደግሞ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ክለብ ተጫውቶ ያሳለፈው የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ድንቅና ምርጥ የግራ መስመር የኮሪደር ስፍራ ተጨዋች የሆነው ሰይፈ ውብሸት ፕሮም የአሁን ሰዓት ላይ በዓለምም ሆነ በሀገራችን ከፍተኛ ወረርሽኝ እየሆነ በመምጣት ላይ ላለው እና የብዙ ሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ለሚገኘው የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ይውል ዘንድ ለሀገሬ እና ለህዝቤ አለውልሽ በሚል ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ300 ሺ ብር ጥሬ ገንዘብና ለ200 ሰዎች የሚሆን ደግሞ 200 ሺ ብር የሚያወጣ ቁሳቁስን የረዳ ሲሆን በወላጅ እናቱ አማካኝነት ደግሞ በተወለደበት የበረንዳ አካባቢ በሚገኘው የ02 ቀበሌ አካባቢም እስከ 15 ኩንታል የሚደርስ የእህል እርዳታ ድጋፍን ማድረጉ ታውቋል።
የኢትዮጵያ ታዳጊ እና የዋናው ብሄራዊ ቡድን የቀድሞው ምርጥ ተጨዋች ሰይፈ ውብሸት ፕሮም የአሁን ሰዓት ላይ ኑሮውን በስዊዘርላንድ ሎዛን ከተማ ያደረገ ሲሆን ከሀገር ከወጣ 20 ዓመታትን ያስቆጠረ ቢሆንም ወደ ኢትዮጵያ በሚመጣ ሰዓት ለተቸገሩ የቀድሞ ስፖርተኞችም በየጊዜው የተለያዩ እርዳታዎችን እንደሚያደርግም ይታወቃል።


ሰይፈ ውብሸት በተጨዋችነት ዘመኑ ከኤሌክትሪክ ጋር የመጀመሪያውን የፕሪምየር ሊግ ዋንጫ ያነሳ ተጨዋች ሲሆን ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋርም የዚህ ዋንጫን ያነሳም እንደሆነ ይታወቃል።
6 ቁጥር ለባሹ ሜዳ ላይ በግራ እግሩ በሚያሳየው ታምራዊ እና የማይጠገብ የኳስ ብቃቱ እንደዚሁም ደግሞ በጥቁረቱ እና መብራት ሀይል እያለ ደግሞ በነጩ የቡድኑ መለያ ወደ ሜዳ በሚገቡበት ሰዓት ይሄ ተጨዋች ከእነ መልኩና አጨዋወቱ የብላክ ስታሮቹን አጨዋወት ይመስላል በሚል በዛን ጊዜ ጋናዎች ጥሩ ጨዋታን ይጫወቱ ነበርና ሰይፈን ጋናዊ ነው እንዴ እስከማለት ደረጃ በመድረስ በርካታ አድናቂዎችንም በችሎታው አትርፎ የነበረ ሲሆን ወደ ስዊዘርላንድም ከባለቤቱ ወለላ ጋር ካመራ በኋላም በእዛው ሀገር ላይ ለሚገኝ ቡድን ኳስን መጫወት በጀመረበት ወቅትም በጊዜው ሪያል ማድሪድ ሎዛን ላይ ትራንዚት ሲያደርግ ዚዳንንም ሆነ ሪያል ማድሪድን በተቃራኒነት መግጠሙም ታውቋል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተጨዋች እንደ ሀገራችን ማህበራት እና ግለሰቦች እሱም የበኩሉን እርዳታና ድጋፍ በማድረጉ ሊመሰገን ይገባል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By መሸሻ ወልዴ
Follow:
Editor at Hatricksport website
Previous Article የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ደጋፊዎች ማህበር ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ እርዳታ አሰባሰቡ
Next Article ሀዋሳ ከተማ ስራ አስኪያጁን አሰናብቶ የክለቡን ፀሀፊ በጊዚያዊነት ቀጥሯል!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የዝውውር ዜናዎችዜናዎችባህርዳር ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

ኦሴ ማዉሊ የጣና ሞገዶቹን ተቀላቅሏል!!

Ermias Misganaw By Ermias Misganaw 5 years ago
ካፍ ውድድሩን ማራዘሙን ይፋ አደረገ !
የጨዋታ ዘገባ | ቡናማዎቹ ወደ አሸናፊነት ተመልሰዋል !!
 ዜና ኮንፌዴሬሽን ካኘ | ዚማሞቶ ኢትዮጵያ ከደረሰ 3ኛ ልምምዱን ዛሬ ሰርቷል።
ዋልያዎቹ መስከረም 2 መቐለ ይገባሉ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
Welcome Back!

Sign in to your account

Lost your password?