መነሻ ገጽ ዜናዎች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተጨዋች ሳምሶን ሽፈራው /ጆሮ/
ዜናዎች

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተጨዋች ሳምሶን ሽፈራው /ጆሮ/

አጋራ
አጋራ

በመሸሻ ወልዴ /G.BOYS/

“በእዚህን ወቅት አስባችሁኝ ላደረጋችሁልኝ ስጦታ በጣም አመሰግናለው”

የእግር ኳስን በክለብ ደረጃ ለኢትዮጵያ ቡና ለቅዱስ ጊዮርጊስ ለሰሚት ለወንጂ ስኳር እና ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጫውቶ ያሳለፈው ዓመለ ሸጋው እና ፈጣኑ የኮሪደር ስፍራው ተጨዋች ሳምሶን ሽፈራው /ጆሮ/ በአሜሪካንም ሆነ እዚሁ በአዲስ አበባ ከተማ ላይ የሚገኙት የቀድሞ ጓደኞቹም ሆኑ የእግር ኳስንም አብረዉት የተጫወቱት ተጨዋቾች በተጨዋችነት ዘመኑ ለሀገር ላበረከተው አስተዋፅኦ በማሰብ ግምቷ ግማሽ ሚሊየን የምትደርስ የመኪና ስጦታ ያበረከቱለት ሲሆን ይኸው ዓመለ ሸጋም ተጨዋች ለተደረገለት የመኪና ስጦታ ሁሉንም ጓደኞቼንም ሆነ በማስተባበሩ ላይ ለተሳተፉት ከፍተኛ ምስጋናዬን በፈጣሪ ስም አቀርብላቸዋለሁም ብሏል።
የእግር ኳስ ጨዋታ ዘመኑ ላይ በቀኝ የኮሪደር ስፍራ ላይ ፈጣን የማጥቃት እንቅስቃሴን በማድረግ ለአጥቂዎች የግብ ኳስ ለማቀበል ከፍተኛ ጥረት ያደርግ የነበረው እና በኢትዮጵያ ቡና ክለብ የተጫዋችነት ዘመን ቆይታውም ቡና የሱዳኑን ክለብ ባሸነፈበት የአዲስ አበባ ጨዋታው ላይ የመጀመሪያ ኢንተርናሽናል ጎሉን ለቡድኑ ያስቀጠረው ሳምሶን ከኳሱ ባሻገር በቀልደኝነቱም የሚታወቅ ሲሆን በእዚህ አስቸጋሪ ወቅት ላይ የተደረገልኝ የመኪና ስጦታ በእውነቱ በጣም ያስደሰተኝ እና ለውለታቸውም ፈጣሪ ብድራቸውን ይክፈልልኝም በማለት ሀሳቡን ቋጭቷል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...