የኢትዮጵያ ከ17 እና ከ20ዓመት በታች የሴቶች ብሄራዊ ቡድኖች በቀጣይ ከኡጋንዳ እና ከቡሩንዲ አቻዎቻቸው ባለባቸው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ምክንያት የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የአንደኛ ዲቪዚዮን ውድድር ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም መደረጉን የሴቶች እግር ኳስ ልማት እና ውድድር ኮሚቴ ዛሬ ታህሳስ 21/2012ዓ.ም ባካሄደው ሳምንታዊ ስብሰባ አሳወቀ፡፡ ውድድሩ ለመራዘሙ ምክንየት በመሆን የቀረበው በርካታ ተጫዋቾች ለብሄራዊ ቡድኑ በየእድሜ ደረጃው በመመረጣቸው መሆኑ ታውቋል፡፡
ባሳለፍነው ቅዳሜ ታህሳስ 18/2012ዓ.ም የተጀመረው የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዲቪዚዮን ውድድር ጨዋታዎች ለ17ዓመት በታች የኢትዮጵያ ሴት ብሄራዊ ቡድን 6ተጫዋቾችን ካስመረጠው የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ቡድን በስተቀር ውድድሮቹ በተያዘላቸው የጨዋታ ፕሮግራም መሰረት እንዲካሄዱ ተወስኗል፡፡
🔗 EFF
አስተያየት ይስጡ