ትግራይ ስታድየም ላይ ተካሂዶ ያለ ምንም ግብ አቻ ከተጠናቀቀው የወልዋሎ እና የሀዋሳ ጨዋታ በኃላ የሁለቱ ቡድን አሰልጣኞች የሰጡት አስተያየት፦
አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ (ወልዋሎ)
ጨዋታው ላይ የተጎዱ ልጆች መኖራቸው እኛጋ ትንሽ ዛሬ የሰው ሀይል ማነስ፣አንዳንድ መጨረስ ሚገበንን እንዳንጨርስ አድርጎናል።አዳዲስ ልጆችን ማግባታችን የልምድ ማነስ ችግር ፈጥሮብናል ሆኖም ግን ይህ ኳስ ጨዋታ ነው ምንም ማድረግ አትችልም።ያገኘናቸው ኳሶችንም መጨረስ አልቻልንም፤በረኛችን ጥሩ ነበረ የመጀመርያ ጨዋታው ነው አንደዚህ ከቀጠለ ኬይታን ማስቀመጥ ሚችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል ስለዚህ ይህ ለኛ ጥሩ ነው ሌሎቹ ግን የልምድ ጉዳይ ባለመኖሩ እንጂ ማሸነፍ ይገባን ነበር።
አሰልጣኝ አዲሴ ካሳ(ሀዋሳ ከተማ)
ጨዋታው ጥሩ ነው።በሁለታችን በኩል የማግባት አጋጣሚዎችን አግኝተን ነበር ነገር ግን ሁለታችንም አልተጠቀምንም።በተለይ እኛ ከሁለት ሽንፈት በኃላ ስለሆነ የመጣነው ከሜዳችን ውጪም ስለነበር በጥንቃቄ ነበር ስንጫወት የነበረው በአጠቃላይ ጥሩ ነበር ጨዋታው።
አስተያየት ይስጡ