ምክትል አሰልጣኝ አስቻለው ሀ/ሚካኤል – አዳማ ከተማ
” እንዳያችሁት በሁለታችንም በኩል ጥሩ የኳስ ፍሰት የታየበት ነው። ከዚህ በፊት ብዙ ጨዋታዎች ላይ ኳስ ተቆጣጥረን ተጫውተን የተሸነፍንባቸው ነበሩ። እነሱን ስህተቶቻችንን አርመን ዛሬ ሶስት ነጥብ ይዘን መውጣት ችለናል።” ብለዋል።
ባህርዳር ላይ ስለገጠማቸው ሽንፈት የተጠየቁት አሰልጣኙ ሲመልሱ “ከአዳማ እና ከአዲስ አበባ ውጪ የሚኖሩ ጨዋታዎች ላይ ዳኞች በተፅዕኖ ነው የሚዳኙት። በራስ መተማመን አይዳኙም። ፌደሬሽኑ ይህንን ጉዳይ ተወያይቶበት መፍትሔ ቢሰጠው ጥሩ ነው።” ብለዋል።
በቀጣይነት ቡድኑ እንደዚህ እንዲቀጥል ምን እየሰራችሁ ነው ተብለው ሲጠየቁም “ያው አሁን እንደምታውቁት ችግር ውስጥ ነን። ችግሩ ይፈታል እያሉን ነው ግን ምንም የተፈታ ነገር የለም። አስተዳደሩ ከጎናችን ቢሆን ትልቅ ውጤት ይዘን እንወጣለን።” በማለት አስተያየታቸውን ቋጭተዋል።
የኢትዮጵያ ቡናው አሰልጣኝ ካሳዬ አራጌ ድህረ ጨዋታ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል ።
አስተያየት ይስጡ