መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና የአሰልጣኞች አስተያየት | ሰበታ ከተማ 2-1 ሀዲያ ሆሳዕና
ሀዲያ ሆሳዕናሰበታ ከተማዜናዎችየአሰልጣኞች አስተያየት

የአሰልጣኞች አስተያየት | ሰበታ ከተማ 2-1 ሀዲያ ሆሳዕና

አጋራ
አጋራ

 

በ12ኛው ሳምንት መርሀግብር አዲስ አበባ ስታዲየም ላይ ሰበታ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን አስተናግዶ በባለሜዳዎቹ 2-1 አሸናፊነት መጠናቀቅ በኋላ። የሰበታው አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ለመገናኛ ብዙሀን አስተያየታቸውን ሲሰጡ የሀድያ ሆሳዕናው አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ ግን አስተያየት ለመስጠት ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ሳናካትት ቀርተናል።

“ውጤቱ ያስፈልገን ነበር ውጤቱ መያዛችን ደግሞ ትልቅ ነገር ነው” (ውበቱ አባተ ሰበታ ከተማ)

ስለጨዋታው

ከባድ ጨዋታ ነው። እነሱ በተከታታይ ነጥብ ጥለው ነው የመጡት። ከወራጅ ለመሸሽ ነው እተጫወቱ ያሉት። እኛም በድሬዳዋ ተሸንፈን ነው እና የመጣነው ጨዋታው ትንሽ ውጥረት የነበረው። ከዛውጭ የጨዋታ መደራረቦች አሉን በዚህም ተጫዋቾቼ ላይ ድክመት ይታያል። ሌላኛው የምንጠቀምብቸው ተጫዋቾች አልነበሩም። ውጤቱ ያስፈልገን ነበር ውጤቱ መያዛችን ደግሞ ትልቅ ነገር ነው።

የዘንድሮ ዕቅዳቹህ

የደረጃ ሰንጠሬዡን ስንመለከት ብዙም የተራራቀ ነገር የለውም። አቅም በሚፈቅደው ደረጃ እስከ መጨረሻ በጥሩ ውጤት መሄድ እንፈልጋለን። እንደ ቡድን የተሻሻሉ ነገሮች አሉ። አሁን ላይ ሆኜ ግን ስለመጨረሻው ቀን መናገር ከባድ ነው። ግን በዚህ አመት ከስጋት ነፃ የሆነ ቡድን ለመስራት ነው እጣርን ያለነው።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...