መነሻ ገጽ ሰበታ ከተማ የአሰልጣኞች አስተያየት ሰበታ ከተማ ከ ፋሲል ከነማ(3-3)
ሰበታ ከተማየአሰልጣኞች አስተያየትየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግፋሲል ከተማ

የአሰልጣኞች አስተያየት ሰበታ ከተማ ከ ፋሲል ከነማ(3-3)

አጋራ
አጋራ

የአሰልጣኞች አስተያየት

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ (ሰበታ ከተማ)

ስለ ጨዋታው

– እግር ኳስ ጨዋታ ዘጠና ደቂቃ ሲደመር ተጨማሪ ሰአት ነው:: ከእረፍት በፊት የተሻለ ነገር ነበረን ከእረፍት በኋላ ደግሞ ፋሲሎች በብዙ ነገር የተሻሉ ነበሩ ::

ከእረፍት በኋላ የተፈጠረው ብልጫ ሁለተኛው አጋማሽ በተጀመረ በመጀመርያዎቹ ሁለት ደቂቃዎች ላይ ያስቆጠሩት ሁለት ጎሎች የራስ መተማመናቸውን ከፍ አድርጎላቸዋል :: ይህ ደግሞ የእኛ የተከላካይ ክፍል መዘናጋት ነው :: ይህም ለረጅም ሰአት ወደ ጨዋታው ለመመለስ ተቸግረን ነበር ::

እኛ የሁለተኛው አጋማሽ የመጀመሪያው ደቂቃ የሰራነውን ስህተት ፋሲሎች በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ ደግመውታል ::

በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ጎል አግብተን መውጣታችን ለእኛ ጥሩ ነገር ነው :: የተጫወትነው ጥሩ ስብስብ ካለው ቡድን ጋር ነው ::

ስለ ደጋፊው

– ጨዋታው ለእኛ ከሜዳ ውጪ ያደረግነው ነው ሊባል የሚችል ነው :: የነበረው ደጋፊ ሙሉ ለሙሉ የፋሲል ነበር ማለት ይቻላል : ለእኛ ጥሩ የሚባል ውጤት ነው ::

ይህ ቡድን ያሳደከው ነው ባሳደከው ቡድን የመቀጣት ያህል ስሜት አልተሰማክም ?

የትም ብትሆን ለእግር ኳሱ ነው የምትሰራው :: እኔ የሰራሁት ነገር አልፋል ::

ቢሆንም ከመጀመሪያው አሰላለፍ ከነበሩት አስራ አንድ ተጫዋቾች አስሩ የነበሩ ልጆች ናችው :: ነባር ቡድንን መግጠም ከባድ ነው እኔም ሰራሁት ሌላ ሰው ያንን ከባድ ነገር ነው ያየሁት እንጂ ለእኔ ያው ነው :: እዛም እዚም የሚጫወቱት ለአንድ ሀገር ነው ::

አሰልጣኝ ስዩም ከበደ (ፋሲል ከነማ)

ስለ ጨዋታው

የመጀመሪያው አጋማሽ እኔ እንደጠበኩት አይደለም ያንንም እረፍት ሰአት ላይ ብዙ ተነጋግረናል ያንንም ብዙ አርመናል ::

ሁለተኛው አጋማሽ አጀማመራችን በጣም ጥሩ ሆኖ ሳለ ከነበረብን መከላከል የተሻለ ነገር ለማድረግ ጥረናል ::

የባከነ አራት ደቂቃዎች እስኪጨመር 3 ለ 1 እየመራን ነበር :: ኳስ ጨዋታ ይህ ነው : ለብዙ የሚያስተምር ነው ለሀገራችን ክለቦች ብቻ ሳይሆን ለአለምም የሚተላለፍ ቢሆን ይህ አስተማሪ ነገር ነው ::

ጨዋታ ማለት ዘጠና ደቂቃ እስከ አልጨረስከው ድረስ ትርጉም የለውም :: በተለይ የመጨረሻዎቹ ሶስት እና አራት ደቂቃዎች ተጫዋቾቼ ጨርሰናል ብለው በውስጣቸው ደስታ የፈጠሩ ይመስለኛል :: ቦታዎችን ትተዋል ትኩረት ማነስ ነበር:: ከበረኛው ጀምሮ ቦታ አጠባበቃችን ጥሩ አልነበረም ::

ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላም ለተጨዋቾቼ የነገርኳቸው ትልቅ ትምህርት ሊሆነን እንደሚገባ እና በትልቅ ትኩረት ልንጫወት እንደሚገባ ነው ::

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የ30ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች መናፍ ዐወል (አዳማ ከተማ): ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...