መነሻ ገጽ ሰበታ ከተማ የአሰልጣኞች አስተያየት | ሰበታ ከተማ ከ ወላይታ ድቻ (1-0)
ሰበታ ከተማወላይታ ድቻዜናዎችየአሰልጣኞች አስተያየትየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የአሰልጣኞች አስተያየት | ሰበታ ከተማ ከ ወላይታ ድቻ (1-0)

አጋራ
አጋራ

 

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ – ሰበታ ከተማ

• ስለ ጨዋታው

የቡድኑ ፍላጎት የሚያሟላ ነገር ይዘን ለምቅረብ እየሞከርን ነው :: ከማሸነፋቸን በላይ ለማሸነፍ የሄድንበት መንገድ ጥሩ ነው ብዬ ነው የማስበው እንደ አጠቃላይ ግን ቡድኔ መሻሻል አለው ለእኔ መልካም ጨዋታ ነበር ::

• በሁለተኛው አጋማሽ ላይ መከላከል ላያ አተኩራችሃል ለምንድነው ?

አሁንም በምንፈልገው አጨዋወት ውስጥ መዋዥቅ አያለሁ በተለይም ከእረፍት በሃላ በነበረው እንቅስቃሴ ከሃላ መስርትን ከመውጣት ይልቅ ተደጋጋሚ ኳሶች ወደ ፊት ይለቀቁ ነበር ያም ይመስለኛል ::

ከሌሎች ጨዋታዎች የተሻለ ነገር ነው የነበረው በሂደት የሚስተካከሉ ነገሮች ይኖራሉ ::

አሰልጣኝ ገ/ክርስቶስ ቢራራ – ወላይታ ዲቻ

ስለ ጨዋታው

ጨዋታው ሁለት ገፅታ ነበረው ከእረፍት በፊት ተጫዋቾቼ ይበልጥ ወደ ሃላ አፈግፍገው ነበር :: ከእረፍት በሃላ ግን ያንን አርመን የተሻለ ቡድን ይዘን ለመቅረብ ችለናል ::

ነገር ግን ከእረፍት በፊት ይህንን አጨዋወት ይዘን ብንገባ ኖሮ የተሻለ ነገር ይመዘገብ ነበር :: ያ ነገር ከመፈጠሩ በፊት አንድ ግብ ተቆጥሮብን ጨዋታው በዛው ሊጠናቀቅ ችሏል ::

ከእረፍት በፊት ሁለት የመስመር አማካዮቼ ከሃላ የሚነሱ ወደ ፊት መምጣት አለመቻላቸው ጥሩ እንዳንሆን አድርጎናል ::

• ሽንፈቱ የመጣው በእናንተ ድክመት ነው ወይስ በተጋጣሚ ጥንካሬ ?

እኔ ጥንካሬም ነው ድክመትም ነው አልለውም ምክንያቱም ፍፁም ቅጣት ምት ተሰጠ የተገኘውን አጋጣሚ መጠቀም ስለቻሉ ብቻ ነው ሊያሸንፉን የቻሉት ::

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

ገረሱ ሸመና መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቀለ

በሊጉ ለመቆየት እየዳዱ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታዎች ረዳት አሰልጣኝ ሾመዋል። በኢትዮጵያ እግር...

ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...