መነሻ ገጽ ዜናዎች የአሰልጣኝ ስዩም አባተ መታሰቢያ የእግር ኳስ ውድድር ነገ ይጀመራል
ዜናዎች

የአሰልጣኝ ስዩም አባተ መታሰቢያ የእግር ኳስ ውድድር ነገ ይጀመራል

አጋራ
አጋራ

በሞት ላጣነው የሀገር ባለውለተኛው አሰልጣኝ ስዩም አባተ የተዘጋጀው የመታሰቢያ ዋንጫ ነገ ይጀመራል
የኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ ውስጥ በተጨዋችነትም በአሰልጣኝነትም በሙያቸው ትልቅ ግልጋሎትን ለሀገርም ለበርካታ ክለቦችም ሰጥተው ያለፉትን ታላቁን የስፖርት አባት እና በቅርቡ በሞት ያጣናቸውን አሰልጣኝ ስዩም አባተን ለማስታወስ እና ለመዘከር በ 6 የከፍተኛ ሊግ ክለቦች መካከል በስማቸው የተዘጋጀ የመታሰቢያ ውድድር የሚደረግ ሲሆን ይህም ጨዋታ ከነገ ጠዋት አንስቶ በቄራ አልማዝዬ ሜዳ ላይ ይካሄዳል።
በአሰልጣኝነት የህይወት ዘመናቸው በክለብ ደረጃ ኢትዮጵያ ቡናን እና በርካታ ክለቦችን እንደዚሁም ደግሞ የብሄራዊ ቡድናችንን በማሰልጠን በሚሰሩት ጥሩ ቡድን በብዙዎች ዘንድ የሚደነቁት እና በተጨዋችነት ዘመናቸውም ለቅዱስ ጊዮርጊስ በመጫወት ከፍተኛ እውቅናን ያገኙት እኚሁ ባለሙያን ለማሰብ ነገ በሚደረገው የመክፈቻ ጨዋታ በቅድሚያ የሚጫወቱት ቡድኖች የቀድሞ የኢትዮጵያ ቡና ተጨዋቾች ከቄራ አንበሳ የጤና ቡድን ሲሆን በመቀጠል የሚደረገው ጨዋታ ደግሞ በ 6 የብሄራዊ ሊግ ክለቦች መካከል የሚደረገው ነው።
የአሰልጣኝ ስዩም አባተ መታሰቢያ የእግር ኳስ ውድድር ሙሉ ፕሮግራም የሚከተለው ሲሆን ጨዋታዎቹን የስፖርት አፍቃሪዎች ከነገ አንስቶ በቄራ አልማዝዬ ሜዳ እንዲከታተሉም በአዘጋጁ አካል ተጋብዘዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...