በዮሴፍ ከፈለኝ
የሰሞኑ ትልቁ መነጋጋሪያ ማነው ከተባለ
አርቢትር ኢያሱ ፈንቴ ቅድሚያውን ይወስዳል፡
፡ በወልዋሎ ቡድን መሪ ማሩ ገ/ፃዲቅ ከተደበደበ
- ማሰታውቂያ -
በኋላ የሁለቱ ምስል በውጪም በሀገር ውስጥም
ኳስ በሚወዱም ሆነ ደንታ በማይሰጠው
የህብረተሰብ ክፍል ትኩረት የሳበ ክስተት ሆኖ
አልፏል፡፡ ባለፈው ሀሙስ ከመቀሌ ኤፍ ኤም
ጋዜጠኛ ነኝ ካለው ጋዜጠኛ ዮናስ ጋር ቆይታ
ያደረገው ኢያሱ አነጋጋሪ ምላሽ ሰጥቷል፡፡
ሁሉም ሲሮጡ ሊደበድቡኝ ነው ብለህ
ታምናለህ የተባለው ኢያሱ የሮጡት ታዲያ
ሊስሙኝ ነው? ማሩ ያልቻለው ተጨዋቾቹ
ስሜታቸውን ተቆጣጥረው ዝም ሊሉኝ ነው
ሲል ያልተጠበቀ ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ከምትሮጥ
ቀይ ካርድ አትመዝም ወይ ሲባል በዚያ ከበባ
ውስጥ ካርድ ዋጋ አለው? እኔ ደግሞ ቆሜ
መደብደብ አልሻም እንደ ወልዲያው ልጅ
እንዲገጥመኝ አልፈልግም፡፡ ሰርቼ የምበላ ሰው
ነኝ ማንንም ሰው አሳክሙኝ የምለው የለም
ልጁ ገና እየተለመነለት ነው ሲል የተሰማውን
ተንፍሷል፡፡ የሀትሪኩ ዮሴፍ ከፈለኝ አርቢትሩ
እንዴት ዳግም ተናገረ? የተናገረውስ በርግጥ
አርቢትር ኢያሱ ፈንቴ ነው? ለሚለው ጥያቄ
ምላሽ ለማግኘት ከአርቢትሩ ጋር ያደረገው
ቆይታ ይህን ይመስላል፡፡
ሀትሪክ፡- ለትግራይ ኤፍ ኤም ጣቢያ
የሰጠኸው ቃለ ምልልስ አለ?
ኢያሱ፡- አንድ ልጅ ደውሎ ጠይቆኝ
መልሻለው ጋዜጠኛ ግን አይደለም፡፡ የሆነ ወሬ
አውርቶኛል፡፡
ሀትሪክ፡- የውይይታችሁ አንኳር ምን
ነበር?
ኢያሱ፡- የትግራይ ህዝብ ይቅርታ
ሊጠይቅህ ይፈልጋል አለኝ፡፡
ሀትሪክ፡- በርግጥስ ህዝቡ ይቅርታ መጠየቅ
ነበረበት?
ኢያሱ፡- የለበትም የትግራይ ሕዝብ ለምን
ይቅርታ ይጠይቀኛል? ኳስ የማያውቅ ሰው
በፈጠረው ችግር ሕዝቡ ይቅርታ መጠየቅ
አይጠበቅበትም፡፡ እኔ ደግሞ ከትግራይ ሕዝብ
ጋር ፀብ የለኝም፡፡ ህዝቡ ደግሞ ምንም
አላደረገኝም አልኩት፡፡
ሀትሪክ፡- ስለ ወልዋሎ ያወራኸው ነገር
አለ?
ኢያሱ፡- አዎ! ምንም አይነት ችግር
በሌለበት ወቅት ወልዋሎ ላይ ሪጎሬ ሰጥቼ
ምንም አልተባልኩም፡፡ አሁን ምን ተገኘ?
ወልዋሎ ሪጎሬ ተሰጥቶበትም አዲስ አበባን
አሸንፎ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ አለፈ ዛሬ ምን
ለወጣቸው ብዬዋለው፡፡
ሀትሪክ፡- ዳኛ ግን ለሚዲያ ማውራት
ይችላል?
ኢያሱ፡- ስለጨዋታውኮ አላወራውም፡
፡ የተበደልኩት እኔ ነኝ፡፡ ስለተጎዳው ስሜቴ
ባወራ ተገቢኮ ነው፡፡ ልጁ ጋዜጠኛ ነኝ
አላለኝም፤ ለአካባቢው ህብረተሰብ ስለምቀርብ
ነው የማወራህ ብሎኛል፡፡
ሀትሪክ፡- ወደ ዳኝነት የመመለስ እድሉና
ፍላጎቱ አለህ?
ኢያሱ፡- እስካሁን አልተመደብኩም
እነርሱም አልመደቡኝም እኔም አልፈለኩም፡፡
የፍርድ ቤት ጉዳይ ስላለኝ እርሱን መጨረስ
እፈልጋለው ጠቅላላ የጤና ምርመራ ማድረግ
አለብኝ፡፡ ፌዴሬሽኑ የወልዋሎን መጨረሻ
ማየትና ከዚያ በኋላ የራስህ ጉዳይ ሊለኝ ነው
የሚፈልገው፡፡ ይህን ጉዳይ አስቀድሜ መጨረስ
እፈልጋለው፡፡ ፌዴሬሽኑ ውድድሩ እንዲጀመር
ነው የሚፈልገው እንጂ የኔን ጉዳይ ማስተካከል
አይፈልግም፡፡ እያጫወትኩ ጉዳዩን መከታተል
ብፈልግም በቅርቡ በሰጠሁት አስተያየት ደስተኛ
የሆነ አይመስለኝም፡፡ ቀሪ ጊዜ አለኝ ለማጫወት
አልጓጓም፡፡
ሀትሪክ፡- በቀጣይ የፌዴሬሽኑን የዳኛ
ኮሚቴን የማናገር እቅድ የለህም?
ኢያሱ፡- ብዙም ማናገር አላሰብኩም በየ3
ሳምንት ወይም 4 ሳምንት የዳኝነት ምድብ
ስለሚደረስ እኔም በቅርቡ በማጫወቴ ብዙም
አልጠብቅም ለማንኛውም አመሰግናለሁ፡፡
ሀትሪክ፡- ትክክለኛ ሪፖርት ግን ፅፈሃል?
ኢያሱ፡– ሪፖርቱ ተቀይሯል የሚል ወሬ
ሰምቻለው አንድ ጋዜጠኛ መጀመሪያ የፃፈው
ሪፖርት ይህ ነው ጫና ተደርጎበት የፃፈውም
ሁለተኛው ሪፖርት ይሄ ነው ብሎ አንቧል
አሉ፡፡ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ጉዳዩን ለማጣራት
እኔን፣ 4ኛው ዳኛና ኮሚሽነሩን ሰኞ 9 ሰዓት
ላይ ጠርቶናል፡፡ (ኢንተርቪው የተሰራው ቅዳሜ
ማታ ላይ ነው)
ሀትሪክ፡- ሪፖርትህ ላይ ሁኔታውን
የገለፅክበት መንገድ ምን ይመስላል?
ኢያሱ፡- ቆይ ላንብልህ… በ2ኛው አጋማሽ
ጊዜ በ72ኛ ደቂቃ ላይ የስታዲየም ፓውዛ
የጠፋ ሲሆን መብራቱ እስኪበራ ጨዋታው
ለ16 ደቂቃ ያህል ተቋርጧል፡፡ መብራቱ ከመጣ
በኋላና ጨዋታው ቀጥሎ በ84ኛ ደቂቃ ቁጥር
27 የሆነው የመከላከያው ፍፁም ገ/ማርያም
የመታት ኳስ የጎሉ የውስጥ መስመር ያለፈ
ሲሆን እኔም ከቁጥር 2 ረዳት ጋር በመናበብ
ወደ መሀል ሜዳ ባመለከትን ጊዜ የወልዋሎ
ግብ ጠባቂ ኳሷን ይዞ የመሃል ዳኛ በሆንኩት
ኢያሱ ፈንቴ ላይ ከሁሉም የቡድን ጓደኞች
ጋር በመሰብሰብ ቁጥር 1 በረከት አማረ፣
ቁጥር 3 አለምነህ ግርማ፣ ቁጥር 5 አሳሪን
አልማሀዲን፣ ቁጥር 9 ማናዬ ፋንቱ፣ ቁጥር
21 በረከት ተሰማ፣ ቁጥር 24 አፈወርቅ ኃይሉ
ተብለው የተዘረዘሩት ተጨዋቾች ከሜዳ ውጪ
ለመደባደብ እያሯሯጡ ካስወጡኝ በኋላ ምክር
መስጫው ላይ ከነበሩትና ተቀይሮ የወጣው
ቁጥር 16 ዋለልኝ ገብሬ በቀጥታ ወደኔ
በመምጣት ድብደባ ፈፅመውብኛል፡፡ የቡድን
መሪው አቶ ማሩ ገ/ፃዲቅ ከተጠባባቂ መቀመጫ
ተነስተው በመምጣት ድብደባ ፈፅመውብኛል፡፡
የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነ ማርያም፣
ም/ል አልጣኝ ሃብቶም ኪሮስና የቡድኑ ወጌሻ
ቢኒየም ተፈሪ እነዚህ ሁሉ የድብደባው አካል
ነበሩ፡፡ ከድብደባው በኋላ ውደድሩን ለመምራት
የጤና ችግር ስለገጠመኝ ቀሪውን 6 ደቂቃ
ውድድሩን መምራት ባለመቻሌ ጨዋታው
ሊቋረጥ ችሏል፡፡ በመጨረሻው የመከላከያው
ቁጥር 10 ዳዊት እስጢፋኖስ ቁጥር 27 ፍፁም
ገ/ማርያም እና የወልዋሎው ቁጥር 4 ተስፋዬ
ደበበ እኔን ከድብደባ ለማትረፍ ብለው ለከፈሉት
መስዋዕትነት ሊመሰገኑ ይገባል ብዬ ፃፍኩ፡፡
ነገር ግን የቡድኑ አሰልጣኝ ም/ል አሰልጣኘና
ወጌሻው አልተቀጡም፡፡ እንደማውቀው ሁለቱ
ረዳቶች፣ ኮሚሽነሩ፣ አራተኛው ዳኛና እኔ
በጋራ 5 ደብዳቤ ፅፈናል ምናልባት 4ኛው ዳኛ
ጋር ይቀየር አይቀየር የማውቀው ነገር የለም፡
፡ ሁላችንም ፅፈን ለኮሚሽነሩ ይድነቃቸው
(ቦቸራ) ነው የሰጠነው፡፡ የኔ ሪፖርት በራሴ
ማህተም የተረጋገጠ ነው፡፡ በሁለት ኮፒ
ስላሰራሁ ፌዴሬሽን ያለውና የያዝኩትን
ማስተያየቴ አይቀርም፡፡ 4ኛ ዳኛው ብቻ ነው
በእስክሪብቶ የፃፈው፡፡
ሀትሪክ፡- በቀጣይ ምን ለማድረግ አሰብክ?
ኢያሱ፡- ፊፋ በተደጋጋሚ ኮርስ ጥቶኝ
ወስጃለው፡፡ ዌብሳይታቸውን ስለማውቅ
ከቪዲዮ ጋር አያይዤ የተቀጡትና ይግባኝ
ሰሚ የወሰነውን ጨምሬ ምናልባት ውሳኔው
ተገቢ አይደለም ብዬ ካመንኩ ለፊፋ ለመላክ
ተዘጋጅቼያለሁ፡፡
ሀትሪክ፡- የተጨዋቾቹ ቅጣት ቢቀነስ
ወይም ቢነሳላቸው…. ያንተ ምላሽ ምን
ይሆናል?
ኢያሱ፡- በጣም ይገርመኛል በጣም ነው
የምስቀው ይህን ካደረጉ በቀጣይ የሚሆነውን
አብረን እናያለን፡፡


