መነሻ ገጽ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተጫዋቾች ምዝገባ የመረጃ አያያዝ ስልጠና ለፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሊሰጥ ነው፡፡
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የተጫዋቾች ምዝገባ የመረጃ አያያዝ ስልጠና ለፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሊሰጥ ነው፡፡

አጋራ
አጋራ

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ለሚሳተፉ ክለቦች የተጫዋቾች ዝውውር ምዝገባ (Transfer Match System) ባለሙያዎች የተጫዋቾች ምዝገባ የመረጃ አያያዝ በተመለከተ ለሁለት ቀናት የሚቆይ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ረቡዕ የካቲት 4/2012 መስጠት እንደሚጀምር አሳወቀ፡፡
ስልጠናው 16ቱም ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች በስራቸው የሚገኙ ተጫዋቾችንና የክለቡ አባላትን መረጃ ወደ አለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ባዘጋጀው /FIFA Connect Platform/ የመረጃ ቋት ሙሉ መረጃ ማስገባት እንዲችሉ የሚያደርግና
በኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት አስተማማኝ እና የተሟላ የተጫዋች ምዝገባ መረጃን መያዝ የሚያስችል ሆኖ ይህ ስርዓት የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስ የሀገር ውስጥ የዝውውር ስርዓቶችንና የተጨዋች መመዝገቢያ ስርዓቶችን በዓለም አቀፍ ዝውውሮችና ምዝገባዎች ወቅት ለግንኙነትና መረጃ ልውውጥ ምቹ ሁኔታዎችን የሚፈጥር ስርዓት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚገኙ 16 ክለቦች የሚሳተፉበት ስልጠና የካቲት 04 እና 05/2012 ዓ/ም ለሁለት ቀን በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ፅ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ የሚከናወን ይሆናል፡፡

via – EFF

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የ30ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች መናፍ ዐወል (አዳማ ከተማ): ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...