መነሻ ገጽ Covid-19 የብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ብቃታቸውን ጠብቀው እንዲቆዩ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን አሰልጣኝ አብርሐም መብራህቱ ገለጹ፡፡
Covid-19ዋልያዎቹዜናዎች

የብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ብቃታቸውን ጠብቀው እንዲቆዩ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን አሰልጣኝ አብርሐም መብራህቱ ገለጹ፡፡

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በዚህ አስቸጋሪ ወቅት በአካልም ሆነ በሥነ-ልቦና እንዳይጎዱና ጥንካሬአቸውን ጠብቀው መቆየት እንዲችሉ ለማድረግ ከቡድኑ አባላት ጋር በጋራ እየሠሩ መሆኑን አስታወቁ፡፡ ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የቀትር የስፖርት ዜና ጋር ቆይታ ያደረጉት የብሄራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አብራሃም መብራህቱ እንደገለጹት ተጫዋቾቹ በአካልም ሆነ በሥነልቦና ጥንካሬአቸውን ይዘው እንዲቆዩ ለማድረግ በኢንተርኔት አማካኝነት በየዕለቱ እየተገናኙ እንደሚሠሩ ተናግረዋል፤ ለዚህም የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አምበል ሽመልስ በቀለ እንዲሁም ምክትል አምበሉ አስቻለው ታመነ ፕሮግራሙን በማስተባበርና በመቆጣጠር ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አሰልጣኙ እንዳሉት እያንዳንዱ ተጫዋች የዕረፍት ጊዜውን ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግና መጻህፍትን በማንበብ እንዲያሳልፉ በማድረግ ላይ እንደሆነና አንድ ተጫዋች በሁለት ሳምንታት ውስጥ ቢያንስ አንድ መጽሃፍ በማንበብ ሪፖርት እንዲያደረግ በማድረግ ተጫዋቾቹ በሥነ-ልቦናና በዕውቀት ራሳቸውን እንዲያሳድጉ እየረዱ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡
እንደአሰልጣኙ ገለጻ ፕሮግራሙ የኮሮና በሽታ ከምድራችን ተወግዶ ተጫዋቾቹ ወደሜዳ ሲመለሱ ከነብቃታቸው እንዲመለሱ ይረዳቸዋል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...