መነሻ ገጽ ዜናዎች የባየርሙኒክ እግር ኳስ ክለብ ያዘጋጀው የእግር ኳስ አሰልጣኞች ስልጠና ዛሬ ተጀመረ፡፡
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የባየርሙኒክ እግር ኳስ ክለብ ያዘጋጀው የእግር ኳስ አሰልጣኞች ስልጠና ዛሬ ተጀመረ፡፡

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከጀርመኑ ባየርሙኒክ እግር ኳስ ክለብ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የ2ኛ ዙር የጀማሪ እግር ኳስ አሰልጣኞች ስልጠና ዛሬ የካቲት 9 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም መሰጠት ጀመረ፡፡


የተለያዩ ሥልጠናዎችን ለመስጠት ወደ አዲስ አበባ የገባው የባየርሙኒክ እግር ኳስ ክለብ ከየካቲት 9 – 13/2012 ዓ.ም ለአምስት ተከታታይ ቀን የሚቆየውን የ2ኛ ዙር የጀማሪ የእግር ኳስ አሰልጣኞች ስልጠና በዛሬው እለት መስጠቱን ጀምሯል፡፡ በዚሁ ስልጠና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል የጽሕፈት ቤት ኃላፊ እና የእግር ኳስ ልማት ኃላፊ የሆኑት አቶ ሰለሞን ገብረስላሴ የመክፈቻው ኘሮግራም ባደረጉት ንግግር የባየርሙኒክ እግር ኳስ ክለብ ያዘጋጀው ይህ ስልጠና በእግር ኳሱ ላይ እየሰሩ ለሚገኙት ወጣት አሰልጣኞች እንዲሁም ለአገራችን እግር ኳስ እድገት ጠቃሚ በመሆኑ በተጨማሪም ባየርሙኒክ በቀጣይ ለመስጠት ባዘጋጃቸው የተለያዩ ስልጠናዎች በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስም አመስግነዋል፡፡


ሠልጣኞችም በመጀመሪያው ዙር የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ለዛሬው ስልጠና በመበቃታችሁ ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ አቅም እንደሚሆናችሁ ተስፋቸውን ገልፀው ስልጠናው በይፋ መጀመሩን አብስረዋል፡፡


ሥልጠናው በቪዲዮ የታገዘ የንድፈ ሀሳብና የተግባር ስልጠና ሲሆን በባየርሙኒክ እግር ኳስ ኘሮጀክት ለበርካታ ዓመት እያገለገሉ የሚገኙት የቀድሞው የባቫሪያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የታዳጊዎች እግር ኳስ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት ሚ/ር ክርስቶፎ ሉክ እየተሰጠ ይገኛል፡፡ በዚሁ የሁለተኛው ዙር ስልጠና ቀደም ሲል በሁለት ምድብ በተካሄደው የጀማሪ እግር ኳስ አሰልጣኞች ስልጠና የተግባር ፈተናውን ያለፋ 30 አሰልጣኞች ተካፋይ ሆነዋል፡፡

Via – EFF

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...