መነሻ ገጽ ስሁል ሽረ የቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ |ወልቂጤ ከተማ ከ ስሁል ሽረ
ስሁል ሽረቅድመ ዳሰሳወልቂጤ ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ |ወልቂጤ ከተማ ከ ስሁል ሽረ

አጋራ
አጋራ

ዛሬ በተካሄደ የሰበታ ከተማ ና ወላይታ ድቻ ጨዋታ ጅማሮውን ያደረገው የ6ተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ ነገ ስድስት ጨዋታዎችን ያስተናግዳል።በፕሪምየር ሊጉ ዓብይ ኮሚቴ ትእዛዝ መሰረት እድሳቱን አጠናቆ ለውድድር ዝግጁ በሆነው ወልቂጤ ስታድየም ሚካሄደው የወልቂጤ ከተማ ና ስሁል ሽረ ጨዋታ በዚህ መልኩ ዳስሰን አቅርበንላችኃል።

ወልቂጤ ከተማ ከ ስሁል ሽረ
የጨዋታ ቀን: ቅዳሜ ታህሳስ 25/2012
የጨዋታ ሰዓት: 9:00
የጨዋታ አርቢትር:
ቦታ: ወልቂጤ ስታድየም

በ5ኛው ሳምንት ወልቂጤዎች ወላይታ ድቻን ሲያሸንፋ ስሁል ሽረዎች በበኩላቸው በመጨረሻ ደቂቃ በተቆጠረባቸው ግብ ከአዳማ ከተማ ጋር እኩል ተለያተው ለነገው ጨዋታ ይቀርባሉ።በመሃላቸው የ3 ነጥብ ልዩነት ይዘው ሚገናኙት ሁለቱ ቡድኖች በነገው ጨዋታ በርካታ ተጨዋቾቻቸውን በጉዳት እና በግል ምክንያት ሚያጡ ይሆናል።ወልቂጤዎች አሳሪ ኣልማህዲ፣ቶማስ ምህረቱ፣አዳነ ግርማን ሲያጡ ስሁል ሽረዎች በበኩላቸው ሙሉኣለም ረጋሳ፣ወንድወሰን ኣሸናፊ እና ሃይለኣብ ሃይለስላሰን ማይጠቀሙ ይሆናል።

መስመር ላይ ትኩረት አድርገው ሚጫወቱት ወልቂጤዎች ከጫላ ተሺታ፣ሄኖክ አወቀ በሚነሱ እና ጃኮ አራፋትን ትኩረት ያደረጉ ኳሶችን በመጠቀም እድሎችን ለመፍጠር ሊጫወቱ እንደሚችሉ ይገመታል።ስሁል ሽረዎች በበኩላቸው ከሜዳቸው ውጪ ሲጫወቱ ሚከተሉትን ወደ ኃላ አፈግፍጎ በመልሶ ማጥቃት እድሎችን የመፍጠር የጨዋታ ስልት ይተገብራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በወልቂጤዌች በኩል ባለፈው ጨዋታ ግብ ያስቆጠረው ጫላ ተሺታ እና ጃኮ ኣራፋት በስሁል ሽረዎች የክለቡ ኮከብ ግብ አስቆጣሪ ዲድየር ሌብሪ እና ከቅጣት የተመለሰው ተከላካዩ ዮናስ ግርማይ ከሁለቱም ቡድኖች በኩል በነገው ጨዋታ ልዩነት ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ይገመታል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

ገረሱ ሸመና መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቀለ

በሊጉ ለመቆየት እየዳዱ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታዎች ረዳት አሰልጣኝ ሾመዋል። በኢትዮጵያ እግር...

ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...