መነሻ ገጽ ዜና እረፍት የሞገስ ታደሰ የቀብር ስነስርዓት ዛሬ ተፈፅሟል
ዜና እረፍትዜናዎች

የሞገስ ታደሰ የቀብር ስነስርዓት ዛሬ ተፈፅሟል

አጋራ
አጋራ

በህመም ምክንያት ትናንት  ማክሰኞ ከቀኑ 6:30 በሞት ከዚህ አለም የተለየው ሞገስ ታደስ ዛሬ በቀጨኔ ደብረሰላም መድሀኒአለም ቤተክርስትያን ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት የቀብር ስነስርአቱ  ተፈፅሟል።

 

1983 ዓ/ም አዲስ አበባ በጃንሜዳ አካባቢ የተወለደው የቀድሞ ተጫዋች ሞገስ ታደሰ። ባጋጠመው የጤና እክል በየካቲት 12 ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በትላንትናው ዕለት የካቲት 05/2012 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ባጋጠመው የጤና እክል ምክንያት ለማሳከም እና ወደ ቀድሞ ጤንነቱ ለመመለስ በርካታ የስፖርት ቤተሰቦች ርብርብ ማድረጋቸው ይታወቃል።

ሞገስ ታደሰ ከቅዱስ ጊዮርጊስ C ቡድን ጀምሮ እስከ ዋናው ቡድን እንዲሁም ሲዳማ ቡና፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ፣ አዳማ ከተማ፣ ወልዲያ ከተማ የተጫወተ ሲሆን ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከታዳጊ ቡድን እስከ ዋናው ቡድን በመጫወት። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ስታልፍ የቡድኑ አባልም ነበር።

ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ እና ድህረ-ገፅ በሞገስ ታደሰ ህልፈት  የተሰማትን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀች ለቤተሰቡ እና ወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለስፖርት ቤተሰቡ መፅናናትን ትመኛለች።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...