መነሻ ገጽ መከላከያ የመከላከያው አናጋው ባደግ ይቅርታ ጠየቀ
መከላከያወላይታ ድቻየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የመከላከያው አናጋው ባደግ ይቅርታ ጠየቀ

አጋራ
አጋራ

በመከላከያ የአንድ አመት ውል የነበረው አናጋው ባደግ ያለ ክለቡ ፍቅድ ለወላይታ ድቻ በመፈረሙና ያልተገባ ቃል በመጠቀሙ ይቅርታ ጠይቋል፡፡

አናጋው በተይ ለሀትሪክ እንደተናገረው “የአንድ አመት ውል እንዳለኝ ነግረውኛል ሕጋዊ መሆናቸውም ገብቶኛል ያለነርሱ ፍቃድ ሚዲያ ላይ ወጥቼ በመናገሬ ይቅርታ እጠይቃለሁ” ብሏል፡፡ “ከወላይታ ድቻ አመራሮች ጋር በአካል አውርቻለሁ በደንብ የተረጋገጠ ነገር ሣይኖር ዜናውን የክለቡ ገፅ ላይ አውጥተውታል ሁኔታውን ያጦዘው ይሄ ነው” ያለው ተጨዋቹ “ወላይታ ድቻዎች መልቀቂያ ጠይቀውኝ ውል እንደጨረስኩ በእርግጠኝነት ነግሬያቸው አምነው አስፈርመውኛል፡፡ በቃል ስምምነት ከመከላከያ አመራሮች ጋር ስላወራው እሺ ብለው ይለቁኛል ብዬ ባሰብም ፍቃደኛ አልሆኑም ውል ስላለን መልቀቅም ሆነ መከላከል የነርሱ መብት ነው” ሲል ተናግሯል፡፡

📸 © wolita dicha Fc page

“በአጠቃላይ ክለቡን እወደዋለው የፕሪ ሚየር ሊግ ውል ለከፍተኛ ሊግ አይሰራም ብዬ መናገሬ ሕጉን ካለማወቅ የተደረገ በመሆኑ የክለቡ አመራሮች አሰል ጣኞችና ደጋፊዎችን ይቅርታ እጠይ ቃለሁ” ሲል ለሀትሪክ አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...