መነሻ ገጽ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ በአዳማ ከተማ ተሸነፈ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ በአዳማ ከተማ ተሸነፈ

አጋራ
አጋራ

 

 

17362402_1468172173256572_5166194747390248306_n20ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር ዛሬም ቀጥሎ ሲውል የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሽንፈት አስተናግዷል።

አዳማ ከተማ በሜዳው ቅዱስ ጊዮርጊስን አስተናግዶ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። ዳዋ ሁቴሳ በ81ኛው ደቂቃ በቀድሞ ክለቡ ላይ ብቸኛዋን የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።

17626347_1468118516595271_4632240916165842008_n

ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፈው ሳምንት በመከላከያ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት መሸነፉ አይዘነጋም።

ፈረሰኞቹ ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎችን በመሸነፋቸው ከደደቢት ጋር የነበራቸውን የነጥብ ልዩነት ማስፋት ሳይችሉ ቀርተዋል። 

በአንፃሩ አዳማ ከተማ ደረጃውን ማሻሻል ችሏል።

በሌላ ጨዋታ አዲስ አበባ ላይ ሃዋሳ ከተማን ያስተናገደው መከላከያ 3 ለ 0 ተሸንፏል። 

ጋዲሳ መብራቱ በ22ኛው እና 46ኛው ደቂቃ እንዲሁም ጃኮ አራፋት በ2ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

አርባ ምንጭ ላይ ደግሞ አርባ ምንጭ ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ያደረጉት ጨዋታ በባለሜዳው ክለብ 2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቋል። 

ፀጋዬ አበራ እና አማኑኤል ጎበና ግቦቹን ከመረብ አዋህደዋል።

በነገው እለት ደግሞ በሃዋሳ ስታዲየም በቡና ደርቢ፥ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ ቡና ይጫወታሉ።

ሊጉን ቅዱስ ጊዮርጊስ 35 ነጥብ ይዞ ሲመራ፥ ደደቢት በተመሳሳይ ነጥብ በግብ ክፍያ ተበልጦ ይከተላል።

አዳማ ከተማ በ20 ጨዋታ 34 ነጥብ ይዞ 3ኛ፣ ሲዳማ ቡና በ19 ጨዋታ 33 ነጥብ በመሰብሰብ 4ኛ እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና በተመሳሳይ ጨዋታ 32 ነጥቦች በመያዝ ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አዲስ አበባ ከተማ በ20 ጨዋታ በተመሳሳይ 15 ነጥቦች የደረጃውን ግርጌ ይዘዋል።

ከፍተኛ ግብ አግቢነቱን የደደቢቱ ጌታነህ ከበደ በ16 ጎሎች ሲመራ፣ ሳላዲን ሰይድ፣ ፍፁም ገብረማርያም እና አዳነ ግርማ በእኩል 9 ጎሎች ይከተላሉ።

የደረጃ ሰንጠረዥና ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎችን ይመልከቱ፡፡

 

 



ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪዎች

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ድንቅ የቅጣት ምቶች በነበሩት ጨዋታ ነገሌ ሲያሸንፍ ሀዋሳ በወልዋሎ ነጥብ ጥሏል

7 ጎሎች እና ሁለት ድንቅ የቅጣት ምት ጎሎች በነበሯቸው ሁለት ጨዋታዎች ነገሌ...