መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና የሀዲያ ሆሳዕና ክለብ ቴክኒካል ዳይሬክተር ደቡብ አፍሪካ ስለሚገኙ ከወላይታ ድቻ ጋር ቢሚኖረው ጨዋታ ቡድኑ በህክምና ባለሞያው ብቻ እየተመሩ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ሀዲያ ሆሳዕናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሀዲያ ሆሳዕና ክለብ ቴክኒካል ዳይሬክተር ደቡብ አፍሪካ ስለሚገኙ ከወላይታ ድቻ ጋር ቢሚኖረው ጨዋታ ቡድኑ በህክምና ባለሞያው ብቻ እየተመሩ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

አጋራ
አጋራ

 

በ13ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በሜዳው ወላይታ ድቻን የሚያስተናግደው ሀድያ ሆሳዕና የክለብ ቴክኒካል ዳይሬክተር ፍቅረየሱስ ዳንኤል በትምህርት ጉዳይ ደቡብ አፍሪካ ስለሚገኙ በህክምና ባለሞያው ቢኒያም ተፈራ እየተመሩ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

በትላንትናው ዕለት በቡድኑ ቦርድ ውሳኔ መሰረት አሰልጣኙ ግርማ ታደሰን እና ረዳቶቹን መታገዳቸው ተከትሎ በአንዳንድ ሚዲያዎች ሀድያ ሆሳዕና በህክምና ባለሞያው ቢኒያም ተፈራ እና በከለቡ ዳይሬክተር ፍቅረየሱስ ዳንኤል። እየተመራ ወላይታ ድቻን ይገጥማል የሚሉ ወሬዎቹ በስፋት እየተዘገበ ይገኛል ይህም ፍፁም የተሳሳተ መሆኑን ሀትሪክ ስፖርት ከክለቡ ቴክኒካል ዳይሬክተር ፍቅረየሱስ ዳንኤል ጋር በነበራት አጭር ቆይታ ማረጋገጥ ችላለች።

ሀትሪል ስፓርት ከ ሀድያ ሆሳዕናው ቴክኒካል ዳይሬክተር አቶ ፍቅረእየሱስ ጋር ያደረገችው አጭር ቆይታ።

በቀጣዩ ጨዋታ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመራህ ወደሜዳ ትገባለህ?

በፍፁም እኔ አሁን ደቡብ አፍሪካ ነው ያለሁት የህክምና ባለሙያው ቢኒያም ተፈራ ቡድኑን እየመራ ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል። መንገድ ላይ ስለነበርኩ አዲስ ነገር ካለ እርግጠኛ አደለሁም።

ደቡብ አፍሪካ በምን ጉዳይ ነው የሄድከው?

የፒኤች ዲ (PHD) ትምህርት ለማጠናቀቅ ነው የሄድኩት።

እና ገና ዶክተር አልተባልክም ማለት ነው?

አዎ! ገና የPHD ትምህርቴን እየተከታተልኩ ነው። አንዳንድ ሚዲያዎች ላይ ዶክተር ፍቅረየሱስ እየተባለ ያለው ነገር ትክክል አይደለም።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...