ፋሲል ከተማ ቡድኑን ለማጠናከር በክረምቱ የዝውውር መስኮት ካስፈረማቸው ተጨዋቾች መካከል ከሶስቱ ጋር ዛሬ በስምምነት ተለያይቷል፡፡
ፋሲል ከተማ የተከላካይ ክፍሉን ክፍተት ለመሸፈን የመሃል ተከላካዩን አቤል ውዱን ከአውስኮድ ፡የመሃል ክፍሉን ለማጠናከር ዳዊት እስጢፋኖስን ከኢትዬ ኢለክትሪክ ፡የአጥቂ ክፍሉን ጎል የማግባት አቅም ለማሳደግ ሮበርት ሴንቴንጎን ከናይጄሪያ ቢያስፈርምም፡
ተጨዋቾቹ ከአፄዎቹ ጋር በነበራቸው የ6 ወር ቆይታ ቡድኑን የሚጠበቅባቸውን ያህል መጥቀም ባለመቻላቸው ክለቡና ተጨዋቾቹ ለመለያየት ከስምምነት በመድረሳቸው ውላቸውን በማቋረጥ ዛሬ ተለያይተዋል፡፡
ክለቡ በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ተጨዋቾቹ ስለነበራቸው ቆይታ በማመስገን በሄዱበት ሁሉ መልካም ነገር እንዲገጥማቸው ተመኝቷል፡፡

አስተያየት ይስጡ