መነሻ ገጽ ሀዋሳ ከተማ ዜናውን ለሰራው አካል ደውዬ ጠይቂያለው የተሳሳተ መረጃ ሰምቼ ነው ዜናውን የሰራሁት ይቅርታ ብሎኛል (አምጣቸው ኃይሌ የሀዋሳ ከተማ ረዳት አሰልጣኝ)
ሀዋሳ ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዜናውን ለሰራው አካል ደውዬ ጠይቂያለው የተሳሳተ መረጃ ሰምቼ ነው ዜናውን የሰራሁት ይቅርታ ብሎኛል (አምጣቸው ኃይሌ የሀዋሳ ከተማ ረዳት አሰልጣኝ)

አጋራ
አጋራ

👉👉ስራየን በሰላም በመስራት እያለሁ ሆን ተብሎ ሂይወቴን ለማበላሸት የተሰራብኝ ዜና ነው

👉👉ዜናውን ለሰራው አካል ደውዬ ጠይቂያለው የተሳሳተ መረጃ ሰምቼ ነው ዜናውን የሰራሁት ይቅርታ ብሎኛል

👉👉ክለቡ መረጃ ሳይሰጣቸው ለምን ዜናውን እንደሰሩት አላውቅም

👉👉ዱሬሳ ተጫዋቾች የጠየቋቸውን የተለያዩ ጥያቄዎች ክለቡ መልስ መመለስ ካልቻለ ክለቡን ተረከቡኝ የሚል ደብዳቤ ነው ያስገባው። (አምጣቸው ኃይሌ የሀዋሳ ከተማ ረዳት አሰልጣኝ)

ትላንት የሀዋሳ ከተማው ረዳት አሰልጣኝ እና የቡድን መሪው ዱሬሳ ዱከሙ ሀዋሳ ከተማ ከስራቸው አሰናብቷቸዋል የሚል ዜና መውጣቱ የሚታወስ ሲሆን። ነገር ግን ዜናው ፍፁም የተሳሳተ ነው ሲሉ የክረቡ ረዳት አሰልጣኝ ከሚዲያችን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ የሚከተለውን ብለውናል።

እርሶ ከሀዋሳ ተሰናብተዋል የሚል መረጃ በሚዲያ ተወርቷል እና ምንድነው ያለው ነገር

እኔ በማላውቀው ጉዳይ ከቡዱኑ ጋር ተለያይቷል የሚል መረጃ ወጥቷል። ዜናውን ለሰራው አካል ደውየ ጠይቂያለው የተሳሳተ መረጃ ሰምቼ ነው ዜናውን የሰራሁት ይቅርታ ብሎኛል። እኔም ይህ ይህ የተሳሳተ ዜና ሂወቴን ለማበላሸት ሆን ተብሎ የተደረገ ነው።

ክለቡ መረጃ ሳይሰጥ ዝም ተብሎ በአሉባልታ ወሬ ዜና መስራት በክለቡ ጫና አይፈጥርም

በጣም ጫና አለው እነሱም ክለቡ መረጃ ሳይሰጣቸው ለምን ዜናውን እንደሰሩት አላውቅም። ቀጥታ ደውየ ዜናውን ለፃፈው አካል ደውየለት ነበር ዜናውን አጥፍቼዋለ ይቅርታ ብሎኛል። ቢሆንም መረጃው ብዙ ሰው ጋር ደርሷል ከመቶ ሰው በላይ ነው የደወለልኝ ምን ተፈጠረ ብሎ። በክለቡ ውስጥ ምንም ሳይፈጠር ከተጫዋቾች ጋር አለመስማማታቸውን ተከትሎ ተሰናብተዋል የሚለው መረጃ ሆን ተብሎ የተደረገ ነው።

በአንተ እና ዱሬሳ መሀከል ከክለቡ ጋር ተያይዞ ያለው እውነታ ምንድነው

ዱሬሳ ተጫዋቾች የጠየቋቸውን የተለያዩ ጥያቄዎች ክለቡ መልስ መመለስ ካልቻለ ክለቡን ተረከቡኝ የሚል ደብዳቤ ነው እንጂ ያስገባው። ለሱም ከክለቡ መልስ እየጠበቀ ነው የሚገኘው ከኔም ጋር በተያያዘ ምንም የተፈጠረ ነገር የለም።

ያለህ ቅሬታ ምንድነው

እኔ ያለኝ ቅረታ በጣም ተሰምቶኛል ምክንያቱም ከተጫዋቾቼ ጋር ሳልጣላ ተጣልቷል የተባለ ሲሆን። ከተጫዋቾቼ ጋር ያለኝ ነገር ሰላም ነው። ስራየንም በመስራት እያለሁ ሆን ተብሎ ሂይወቴን ለማበላሸት የተሰራብኝ ዜና ነው።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...