መነሻ ገጽ ወልዋሎ ወልዋሎ የሁለት ተጨዋቾች ዝውውር ሲያጠናቅቅ የግብ ጠባቂውን ውል አራዝሟል
ወልዋሎዜናዎች

ወልዋሎ የሁለት ተጨዋቾች ዝውውር ሲያጠናቅቅ የግብ ጠባቂውን ውል አራዝሟል

አጋራ
አጋራ

 

በክረምቱ የተጨዋቾች ዝውውር በርካታ ተጨዋቾችን ያስፈረሙት ወልዋሎዎች ሁለት የተከላካይ መስመር ተጨዋቾችን አስፈርመዋል።

ባሳለፍነው የውድድር አመት ከአክሱም ከተማ ጋር ያሳለፈው ኤርሚያስ በለጠ ባሳለፍነው ሳምንት ከቡድኑ ጋር ልምምድ ሲያከናውን ከቆየ በኃላ ፌርማውን ለቢጫ ለባሾቹ ማኖር ችሏል።የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና፣ኢትዮ ኤሌክትሪክና የየመኑ ክለብ አልሳቀር ተጨዋች ኤርሚያስ በለጠ በተከላካይ ክፍሉ በርካታ ተጨዋቾችን በያዘው የዮውሃንስ ሳህለ ስብስብ ቀዋሚ ተሰላፊነትን ለማግኘት ብርቱ ፋክክር ይጠብቀዋል።

ተከላካይ ክፍላቸውን በማጠናከር የተጠመዱት አሰልጣኝ ዮውሃንስ ሳህለ በቅርቡ ከሻምፒዮኖቹ መቐለ ጋር የተለያየውን አቼምፖንግ አሞስን የግላቸው ማድረግ ችለዋል።በ2010 በዮውሃንስ ሳህለ አማካኝነት መቐለ 70 እንደርታን የተቀላቀለው አሞስ ከአንድ አመት ቆይታ በኃላ ከቀድሞው አሰልጣኙ ጋር ሚገናኝ ይሆናል።

በተጨማሪ ወልዋሎ ብሩክ ሰሙን ከአዲስ አበባ ከተማ ሁለተኛ ቡድን ሲያስፈርሙ፤ባሳለፍነው ውድድር አመት የክለቡን ግብ ክልል ሲጠብቅ የነበረውን አብዱላዚዝ ኬይታን ውል ለተጨማሪ አንድ አመት አራዝመዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...