ወልዋሎ ዓድግራት ዩኒቨርሲቲ እብዱልአዚዝ ኬይታን አስፈረመ
ግብ ጠባቂ ሲያፈላልጉ የነበሩት ወልዋሎ ዓድግራት ዩኒቨርሲቲ ጊኒያዊውን እብዱልኣዚዝ ኬይታን በኣንድ ዓመት ውል ኣስፈርመዋል።በ2012 ኣፍሪካ ዋንጫ ሃገሩ ጊኒን የወከለው አብዱልአዚዝ በዛምቢያ ሊግ ከክለቡ ቢዩልድ ኮን ጋር የተሳኩ ዓመታትን ማሳለፍ ችሏል።ባለፈው ውድድር ዓመት ዮውሃንስ ሽኩሩ፣በረከት ኣማረ፣ዘውዱ መስፍን ና በለጠ ተስፋዬን እያፈራቁ የተጠቀሙት ወልዋሎዎች በዘንድሮው ዓመት ኢትዮጵያ ፕሪመርሊግ አብድልኣዚዝ ኬይታን በቋሚነት ሊጠቀሙ እንደሚችሉ ይገመታል።
አስተያየት ይስጡ