መነሻ ገጽ ወልዋሎ ወልዋሎ አዲግራት ዮንቨርሲቲ የስድስት ተጨዋቾችን ዝውውር አጠናቋል
ወልዋሎዜናዎች

ወልዋሎ አዲግራት ዮንቨርሲቲ የስድስት ተጨዋቾችን ዝውውር አጠናቋል

አጋራ
አጋራ

 

ከትላንት ወዲያ በተከፈተው የክረምት ወር የተጨዋቾች ዝውውር ላይ በንቃት መሳተፍ የጀመረው ወልዋሎ ሥስት ተጨዋቾችን አስፈርሟል።

የዮሐንስ ሳህሌ ውልን ለአንድ ዓመት ያራዘመው ወልዋሎ ፍቃዱ ደነቀ፣ሳሙኤል ዮውሃንስ እና ራምኬል ሎክን ከድሬዳዋ ከተማ ዘሪሁን ብርሃኑ፣ሚካኤል ለማ ከመድን፣ዳዊት ወርቁን ከ ደደቢት አስፈርሟል።

በያዝነው ዓመት ከድሬዳዋ ከተማ ጋር በጉዳት ምክንያት የተጠበቀውን ይህል ግልጋሎት ያልሰጠው የቀድሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣መቐለ 70 እንደርታና ድሬዳዋ ከተማ ተከላካይ ፍቃዱ ደነቀ ከቀድሞ አሰልጣኙ ጋር እሚገናኝ ይሆናል።ሌላኛው አዲስ ፈራሚ የግራ መስመር ተከላካዩ ሳሙኤል ዮሐንስ ፤በተጠናቀቀው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ውድድር በግራ መስመር ተከላካይነት ከታዩት ተጨዋቾች ሚጠቀስ ነው።

የመስመር አማካኛቸውን ኤፍሬም አሻሞን ለመቐለ 70 እንደርታ አሳልፈው የሰጡት ወልዋሎዎች የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ፣ፋሲል ከነማ፣ድሬዳዋ ከተማና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጨዋች የሆነው ራምኬል ሎክ ኤፍሬም ትቶት የሄደውን የመስመር ክፍል ይሸፍናል ተብሎ ይጠበቃል።

በተጨማሪ ከደደቢት ወጣት ቡድን አድጎ በያዝነው ዓመት ከደደቢት ጋር ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴን ያደረገው ዳዊት ወርቁ ሌላኛው የወልዋሎ ፈራሚ ሆኗል።

በተጨማሪም የመሃል ሜዳቸውን ለማጠናከር ኣሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ዘሪሁን ብርሃኑ፣ሚኪኤለ ለማ ከመድን እስፈርመዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...