የወልዋሎ አዲግራት ተጨዋቾች ከክለቡ ጋር ያላቸውን የደሞዝ ችግር በመፍታት ልምምዳቸውን መጀመራቸው ታውቋል።
ያልተከፈለ የሶስት ወር የተጨዋቾች ደሞዝ ሳይከፍል የቆየው ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሁለት ወር ደሞዝ ሲከፍል ቀሪ የአንድ ወር ደሞዝም በቅርብ ቀን እንደሚከፍል ለተጨዋቾቹ አሳውቋል።
ባልተከፈለ ደሞዝ ምክንያት ተጨዋቾቹ ለአንድ ቀን ልምምድ አቋርጠው የነበረ ሲሆን ከክለቡ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተው ችግሩን በመፍታት ልምምዳቸውን በማድረግ ይገኛሉ።
ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች የተሸነፈው የፀጋይ ኪዳነ ማርያም ቡድን በ3ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሜየርሊግ ቅዳሜ ህዳር 15 ኢትዮጵያ ቡናን ሚገጥም ይሆናል።
አስተያየት ይስጡ