መነሻ ገጽ ወልዋሎ ወልዋሎ አዲግራት አራት ተጨዋቾችን አስፈረመ
ወልዋሎዜናዎች

ወልዋሎ አዲግራት አራት ተጨዋቾችን አስፈረመ

አጋራ
አጋራ

ወልዋሎ አዲግራት አራት ተጨዋቾችን አስፈረመ

በዮሐንስ ሳህሌ እየተመራ ቡድኑን እንደ አዲስ እያዋቀረ እሚገኘው ወልዋሎ አዲግራት የአራት ተጨዋቾችን ፊርማ ማጠናቀቅ ችሏል።

በጉዳት ምክንያት ለአንድ ዓመት ያህል ከሜዳ እርቆ የቆየው አይናለም ሃይሉ ቢጫ ለባሾቹን መቀላቀል ችሏል።ደስታ ደሙና በረከት ተሰማን ያጣው ወልዋሎ አይናለምን ማስፈረሙ ተከትሎ ሁለቱ ተጨዋቾች ትተውት እሚሄዱትን ክፍተት ለመድፈን ሊረዳቸው እንደሚችል ይገመታል።በ2013 የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ወደ አፍሪካ ዋንጫ ባረገው ጉዞ ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከተው የቀድሞው የመከላከያ፣ደደቢት ና ፋሲል ከነማ ተጨዋች አይናለም ሃይሉ ወልዋሎን መቀላቀሉ ተከትሎ ከቀድሞ አሰልጣኙ ዮሐንስ ሳህሌ ጋር በድጋሚ እሚገናኝ ይሆናል።

በተጨማሪ ወልዋሎ ሁለት ናሚቢያውያን አጥቂዎች ማስፈረም ችሏል።አንደኛው ባሳለፍነው የውድድር ዓመት የድሬዳዋን አጥቂ ክፍል የመራው ኢታሙናይ ኬይሙኒ ሲሆን ሁለተኛው ደሞ ጆናስ ሎሎ ይባላል።

መሃል ክፍል ላይ አፍወርቅ ሃይሉ፣አማኑኤል ጎበና ና ብርሃኑ አሻሞን ያጣው ወልዋሎ ጋናዊው ኬኔዲ አሽያን ከኢራቁ ክለብ ዳርባዲንክሃን ማስፈረም ችሏል።

በ2010 ለሲዳማ ቡና ፈርሞ ያልተሳካ ጊዜ ያሳለፈው ኬኔዲ በ2013 የእፍሪካ ዋንጫ ከ20 ዓመት በታች እንዲሁም ዓለም ከ20 ዓመት በታች ውድድር ሃገሩ ጋናን ወክሎ መጫወት ችሏል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...