አሰልጣኝ ደለለኝ ደቻሳን በቋሚነት ከቀጠሩ በኃላ በከፍተኛ መነቃቃት ላይ የሚገኙት ወላይታ ድቻዎች የቀድሞው ተጫዋቻቸውን አማኑኤል ተሾመን ማስፈረማቸው ታውቋል ::
ከድሬድዋ ከተማ ጋር በስምምነት የተለያየው አማኑኤል ተሾመ ማረፊያውን የጦና ንቦቹን በድጋሚ ሲያደርግ ለቡድኑ ትልቅ ሚናን እንደሚጫወት ይጠበቃል ::
አማኑኤል ተሾመ ከዚህ ቀደም ለአዲስ አበባ ከተማ ፤ ወላይታ ድቻ ፤ መከላከያ እንዲሁም ድሬድዋ ከተማ በመጫወት አሳልፏል ::
አስተያየት ይስጡ