መነሻ ገጽ ኮንፌድሬሽን ካፕ ወላይታ ድቻ ለተጫዋቾቹ የገንዘብ ሽልማት አበረከተ
ኮንፌድሬሽን ካፕወላይታ ድቻዜናዎች

ወላይታ ድቻ ለተጫዋቾቹ የገንዘብ ሽልማት አበረከተ

አጋራ
አጋራ

በሃዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ትናንት በተካሄደው የአፍሪካ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወላይታ ዲቻ የግብጹን ዛማሊክን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፉ ትናንት መዘገቡ ይታወሳል።

 

ወላይታ ዲቻ ማሸነፉን ተከትሎ ክለቡ ከ520 ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለእያንዳንዱ ተጫዋች የ20 ሺህ ብር ጉርሻ ማበርከቱን የወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ ቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ጌታሁን ጋረደው ተናግረዋል። 

ሁሉቱ ቡድኖች ያደረጉት ጨዋታ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት አማካኝነት በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲሰራጭ የተደረገ ሲሆን፥ ወላይታ ዲቻም ከቴለቭዥን ስርጭት ሽያጭ 25 ሺህ ዶላር ማግኘቱ ተመልክቷል።

ከዚህ በፊት ዲቻ ከሜዳው ውጭ ሲያሸንፍ ለተጨዋቾች 5 ሺህ ጉርሻ ይሰጣቸው እንደነበረ ያስታወሱት ዶክተር ጌታሁን፥ በአሁኑ ወቅት ገንዘቡ ወደ 20 ሺህ ብር ከፍ እንዲል መደረጉን ገልፀዋል።

በግብጽ በሚደረገው የመልስ ጨዋታ ቡድኑ ካሸነፈ ለተጨዋቾች ተመሳሳይ ሽልማት እንደተዘጋጀ ጠቁመው፥ ሽልማቱ በዚህ ብቻ የሚያበቃ አለመሆኑን ጠቁመዋል። 

ወላይታ ዲቻ ትናንት ያሳየው ብቃት ከሳምንት በፊት ከዛንዚባሩ ዙማሙቶ ክለብ ጋር ካደረገው ጫወታ ጋር ሲነጻጸር በኳስ ቁጥጥር፣ ተግባብቶ በመጫወትና በታክቲክ መሻሻል ተስተወሎበታል።

ወላይታ ዲቻ በጫዋታው የበላይነት የወሰደ ሲሆን በርካታ ደጋፊዎች በሃዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ተገኝተው ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።

የግብጹ ዛማሊክ ከተመሰረተ 107 ዓመት ዕድሜ ያለው ሲሆን በአንጻሩ ወላይታ ዲቻ ደግሞ በ2005 ዓ.ም የተመሰረተ መሆኑ ይታወቃል። 

ወላይታ ዲቻ ከአሥር ቀን በኋላ የመልስ ጨዋታውን ወደ ግብፅ ተጉዞ እሚያደርግ ይሆናል።

Source-Ena

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ሲዳማ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሲዳማ ቡና ቡድን መሪ ታገደ

በዮሴፍ ከፈለኝ የፕሪምየር ሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና የቡድን መሪው የቀድሞው ዳኛ ዕግድ...

ዜናዎችየዲሲፕሊን ውሳኔዎች

27ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አብዱላጢፍ ባምባ (መቐለ 70 እንደርታ) : ክለቡ ከ ወልዋሎ አዲግራት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...