መነሻ ገጽ ሪፖርት ኢትዮጵያ ቡና ድሬዳዋ ከተማን በመርታት የሊጉን ጅማሬ አሳምሯል
ሪፖርትኢትዮጵያ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግድሬዳዋ ከተማ

ኢትዮጵያ ቡና ድሬዳዋ ከተማን በመርታት የሊጉን ጅማሬ አሳምሯል

አጋራ
አጋራ

በሁለተኛ ቀን ውሎ ኢትዮጵያ ቡና የምስራቅ ክልል ተወካዩን ድሬዳዋ ከተማን በአዲስአበባ ስታዲየም 2-1 በሆነ ውጤት በመርታት የሊጉን ጅማሬ በድል ጀምሯል።

በአዲስአበባ ከተማ ዋንጫ ድል ካደረገው ቡድን ቶማስ ስምረቱና ሱልይማን ሉኩዋ ፋንታ ሚኪያስ መኮንን እና ተመስገን ካስትሮን ወደ ሜዳ ይዘው ገብተዋል።በአንፃሩ ድሬዎች በትግራይ ዋንጫ ያልተጠቀሙባቸውን ግብ ጠባቂው ሳምሶን አሰፋንና አንተህ ተስፋዬን ተጠቅመዋል።

በመጀመሪያው የጨዋታ አጋማሽ ጥሩ መንቀሳቀስ የቻሉት ኢትዮጵያ ቡናዎች በ31ኛ ደቂቃ ላይ ሳምሶን ጥላሁን ላይ የተሰራውን ጥፋት ተክተሎ የእለቱ አርቢትር አማኑኤል የሰጡት ፍፁም ቅጣት ምት እራሱ ሳምሶን አስቆጥሮ 1-0 መምራት አስችሏል።

ከግቧ መቆጠር በኃላ ጨዋታው ተጠናቆ በባከነ ሰዓት ኢታሙና ኬይሙኒ ከመስመር በቀጥታ የመታት ኳስ ግብ ተቆጥራ ጨዋታው 1-1 በሆነ ውጤት ወደ መልበሻ ማምራት ችሏል።

በሁለተኛው አጋማሽ ኢትዮጵያ ቡናዎች ሙሉ ሶስት ነጥብ ለማግኘት በሙሉ ሀይል ወደ ጨዋታ መመለስ ችለዋል። ተደጋጋሚ ጨና ፈጥረው መጫወት የቻሉት ቡናዎች ተካለኝ ደጀኔ ያሻማውን ኳስ አሕመድ ረሺድ ሞክሯት የተመለሰችውን ኳስ አቡበከር ናስር ወደ ግብነት ቀይሮ ኢትዮጵያ ቡና ሊጉን በድል የሚጀምርበትን እድል አመቻችቷል።ጨዋታውም በኢትዮጵያ ቡና 2-1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...