ካሳዬ እራጌን በእሰልጣኝነት የቀጠሩት ኢትዮጵያ ቡና የሁለት ወሳኝ ተጨዋቾቻቸውን ውል እራዝመዋል።ባሳለፍነው የውድድር ዓመት 11 ጎሎችን ያስቆጠረው ተስፈኛው ወጣት እቡበከር ነስሩ ከእናት ክለቡ ጋር ለቀጣይ ዓመት ለመቀጠል ተስማምቷል።

በተመሳሳይ በተለያዩ ቦታዎች በመጫወት ሚታወቀው እያሱ ታምሩ ሌላው ውሉን ያራዘመ ተጨዋች ነው።በፓፓዲች እና በጎሜዝ ስር በተለያዩ ቦታዎች በመጫወት ጥሩ ብቃቱን ያሳየው እያሱ በቀጣይ ዓመት በካሳዬ እራጌ ቡድን ቁልፍ ቦታ ሊሰጠው እንደሚችል ይገመታል።
ኢትዮጵያ ቡና በሚቀጥሉት ቀናቶች ውስጥ የነባር ተጨዋቾቹ ውል ማራዘም በተጨማሪም የእዳዲስ ተጨዋች ዝውውር ያጠናቅቃል ተብሎ ይጠበቃል።
አስተያየት ይስጡ