መነሻ ገጽ ኢትዮጵያ ቡና ኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ የጥሎ ማለፍ ውድድርን አስመልክቶ ላቀረበው ጥያቄ ምላሽ ተሰጠ
ኢትዮጵያ ቡናዜናዎችጥሎ ማለፍ

ኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ የጥሎ ማለፍ ውድድርን አስመልክቶ ላቀረበው ጥያቄ ምላሽ ተሰጠ

አጋራ
አጋራ

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2011 ዓ.ም የጥሎ ማለፍ ውድድር ሐምሌ 11 ቀን 2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ ቡና ከ ሐዋሳ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ጋር ለመጫወት ኘሮግራም መውጣቱ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ሐምሌ 5 ቀን 2011 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ ይህንን ጨዋታ ማካሄድ እንደማይችል ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አሳውቋል ፡፡ ፌዴሬሽኑም ይህንኑ መሠረት በማድረግ ለተጋጣሚው ሐዋሳ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በደብዳቤ ለቀጣዩ ጨዋታ ማለፋን ከገለፀ በኋላ የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ በድጋሚ ሐምሌ 8 ቀን 2011 ዓ.ም ለፌዴሬሽኑ በፃፈው ደብዳቤ ቀደም ሲል ሐምሌ 5 ቀን 2011 ዓ.ም መሳተፍ እንደማይፈልግ የገለፀበትን ደብዳቤ በመሻር የጥሎ ማለፋን ውድድር ለማካሄድ ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል፡፡
ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሊግ ኮሚቴ በጉዳዩ ላይ በመወያየት በመጀመሪያው ደብዳቤ የኢትዮጵያ ቡና ያቀረበውን ጥያቄ መሠረት በማድረግ ወስኖ ለተጋጣሚው ቡድን ያሳወቀ በመሆኑ ሐምሌ 8/2011 ዓ.ም የተፃፈውን የጥያቄ ደብዳቤ ያልተቀበለ መሆኑን ዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2011 ዓ.ም በውድድር ዳይሬክቶሬት በተፃፈው ደብዳቤ ለክለቡ አሳውቋል፡፡

Via- eff

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...