በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2011 ዓ.ም የጥሎ ማለፍ ውድድር ሐምሌ 11 ቀን 2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ ቡና ከ ሐዋሳ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ጋር ለመጫወት ኘሮግራም መውጣቱ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ሐምሌ 5 ቀን 2011 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ ይህንን ጨዋታ ማካሄድ እንደማይችል ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አሳውቋል ፡፡ ፌዴሬሽኑም ይህንኑ መሠረት በማድረግ ለተጋጣሚው ሐዋሳ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በደብዳቤ ለቀጣዩ ጨዋታ ማለፋን ከገለፀ በኋላ የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ በድጋሚ ሐምሌ 8 ቀን 2011 ዓ.ም ለፌዴሬሽኑ በፃፈው ደብዳቤ ቀደም ሲል ሐምሌ 5 ቀን 2011 ዓ.ም መሳተፍ እንደማይፈልግ የገለፀበትን ደብዳቤ በመሻር የጥሎ ማለፋን ውድድር ለማካሄድ ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል፡፡
ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሊግ ኮሚቴ በጉዳዩ ላይ በመወያየት በመጀመሪያው ደብዳቤ የኢትዮጵያ ቡና ያቀረበውን ጥያቄ መሠረት በማድረግ ወስኖ ለተጋጣሚው ቡድን ያሳወቀ በመሆኑ ሐምሌ 8/2011 ዓ.ም የተፃፈውን የጥያቄ ደብዳቤ ያልተቀበለ መሆኑን ዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2011 ዓ.ም በውድድር ዳይሬክቶሬት በተፃፈው ደብዳቤ ለክለቡ አሳውቋል፡፡
Via- eff
አስተያየት ይስጡ