መነሻ ገጽ አዳማ ከተማ አዳማ ከተማ ደመወዛችን ተቀነሰ ባሉ 9 ተጨዋቾች ተከሠሠ
አዳማ ከተማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

አዳማ ከተማ ደመወዛችን ተቀነሰ ባሉ 9 ተጨዋቾች ተከሠሠ

አጋራ
አጋራ

 

የ50ሺ ብር ወርሃዊ ደመወዝ ገደብን የሚደነግግ ደንብ መውጣቱ እያወዛገበ ባለበት አዳማ ከተማ ከህጉ መውጣት በፊት ውል የተዋዋላቸውን ተጨዋቾች ደመወዝ በመቀነስ 34 ሺ ብር መክፈሉ ተቃውሞ አስነስቶበታል፡፡

.ወደ 5 ወር የሚጠጋ ደመወዝ ያልከፈለው አዳማ ከተማ የ2 ወር ደመወዝ ሰሞኑን የከፈለ ሲሆን ሁሉንም በ34 ሺ ብር ደመወዝ መክፈሉ ዳዋ ሁቴሳ ከነአን ማርክነህ ምኞት ደበበ ሱሌይማን መሃመድ በረከት ደስታ ቡልቻ ሹራ ብሩክ ቃልቦሬን ጨምሮ በ9 ተጨዋቾች መከሰሱ ታውቋል፡፡ ተጨዋቾቹ ዛሬ ክሳቸውን ለፌዴሬሽን ያስገቡ ሲሆን የክለቡ አዲሱ ስራ አስኪያጅ አቶ ገመቹ መኮንን ስልክ ቢደወልላቸውም ቴክስት ቢደረግላቸውም አለመመለሳቸው የክለቡን አቋም ማወቅ አልቻልንም፡፡ የፌዴሬሽኑ ጊዜያዊ ዋና ጸሃፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ግን “ከህጉ በፊት የነበረው ውል መጣስ የለበትም..በሁለቱ ወገኖች ስምምነት ከሌለ በተናጠል የሚወሰኑ ውሳኔዎችም ተቀባይነት የለውም” ሲሉ የፌዴሬሽኑን አቋም ገልጸዋል::

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...