አዳማ ከተማ የተጫዋቹን ውል አራዘመ !
ከአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ጋር ከተለያዩ በኋላ ከበርካታ ተጫዋቾቻቸው ጋር እየተለያዩ የቆዩት አዳማ ከተማዎች የፊት መስመር አጥቂያቸውን ውል ማራዘማቸው ታውቋል ።
በሊጉ የፊት መስመር ስፍራ ላይ ልምድ ካላቸው መካከል አንዱ የሆነው ሚካኤል ጆርጅ በአዳማ ከተማ ለተጨማሪ አንድ ዓመት ለመቆየት መስማማቱን ለማወቅ ተችሏል ።
ቁመተ መለሎው እና በአካል ብቃት ጥንካሬው የሚታወቀው ሚካኤል ጆርጅ ሊጉ ዳግም ሲጀምር ቡድኑን በአምበልነት እንደሚመራ ሀትሪክ ስፖርት ለማወቅ ችላለች ።
ሚካኤል ጆርጅ ከዚህ ቀደም በሊጉ ሻምፒዮን ደደቢትን ጨምሮ በሙገር ሲሚንቶ ፣ ሲዳማ ቡና ፣ ዳሽን ቢራ እንዲሁም አውስኮድ የተሳካ ጊዜን ማሳለፉ ይታወሳል ።