መነሻ ገጽ አዳማ ከተማ አዳማ ከተማ የተጫዋቹን ውል አራዘመ !
አዳማ ከተማዜናዎችየዝውውር ዜናዎች

አዳማ ከተማ የተጫዋቹን ውል አራዘመ !

አጋራ
አጋራ

 

ከአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ጋር ከተለያዩ በኋላ ከበርካታ ተጫዋቾቻቸው ጋር እየተለያዩ የቆዩት አዳማ ከተማዎች የፊት መስመር አጥቂያቸውን ውል ማራዘማቸው ታውቋል ።

በሊጉ የፊት መስመር ስፍራ ላይ ልምድ ካላቸው መካከል አንዱ የሆነው ሚካኤል ጆርጅ በአዳማ ከተማ ለተጨማሪ አንድ ዓመት ለመቆየት መስማማቱን ለማወቅ ተችሏል ።

ቁመተ መለሎው እና በአካል ብቃት ጥንካሬው የሚታወቀው ሚካኤል ጆርጅ ሊጉ ዳግም ሲጀምር ቡድኑን በአምበልነት እንደሚመራ ሀትሪክ ስፖርት ለማወቅ ችላለች ።

ሚካኤል ጆርጅ ከዚህ ቀደም በሊጉ ሻምፒዮን ደደቢትን ጨምሮ በሙገር ሲሚንቶ ፣ ሲዳማ ቡና ፣ ዳሽን ቢራ እንዲሁም አውስኮድ የተሳካ ጊዜን ማሳለፉ ይታወሳል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...