ዋና አሰልጣኛቸውን ለሀድያ ሆሳዕና አሳልፈው የሰጡት አዳማ ከተማዎች በርካታ ተጫዋቾቻቸው ጋር መለያየታቸውን ቀጥለዋል ።
አሁን ይፋ በሆነ መረጃ በአዳማ የፊት መስመር ጥሩ እንቅስቃሴን ሲያሳይ የቆየው ዳዋ ሆቴሳ ማረፊያውን በሀድያ ሆሳዕና ማድረጉ ተገልጿል ።
በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ የሚመሩት ሀድያ ሆሳዕና በርካታ ቁጥር ያላቸውን ተጫዋቾች ከአዳማ ከተማ በማስፈረም ላይ ይገኛሉ ።
ዳዋ ሆቴሳ በአዳማ የተሳካ ጊዜ ከማሳለፉ አስቀድሞ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት በመጫወት ማሳለፉ ይታወሳል ።
አስተያየት ይስጡ