መነሻ ገጽ አዳማ ከተማ አዳማ ከተማ በዘጠኝ ነባር ተጨዋቾች ተከሰሰ
አዳማ ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

አዳማ ከተማ በዘጠኝ ነባር ተጨዋቾች ተከሰሰ

አጋራ
አጋራ

አዳማ ከተማ የ9 ነባር ተጫዋቾችን ህጋዊ ክፍያ አልከፈለም በሚል በተጨዋቾቹ ቅሬታ ቀረበበት፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እስከ ሐምሌ 5/2012 ድረስ የተጨዋቾቹን ተገቢ ክፍያ ከፍለው አልጨረሱም በሚል ከማንኛውም የዝውውር ሂደት ካገዳቸው 6 ክለቦች መሀል አንዱ የሆነው አዳማ ከተማ የማንኛውም ተጨዋች ደመወዝ ከ5ዐ ሺህ በር መብለጥ የለበትም የሚለው ሕግ ሳይፀድቅ በፊት የነበረን ውል በመሻር በአዲሱ የደመወዝ ክፍያ እየከፈለ መሆኑን ነባር ተጨዋቾቹን አስቆጥቷል፡፡

“በነባር የውል ስምምነቴ የሚከፈለኝ 15ዐ ሺህ ብር ነው አዲሱ ሕግ አይመለከተኝም፤ አየከፈሉ ያለው ግን 34 ሺህ ብር ብቻ ነው፤ ይሄ ሕገ ወጥ ተግባር ነው፤ ገና የ6 ወር ክፍያ አልተከፈለኝም በማለት ዳዋ ሁቴሳ ለሀትሪክ ተናግሯል፡፡ በነባሩ ውል የፈረሙ ወደ 9 ተጨዋቾች መሀል ለጊዮርጊስ የፈረመው ከነአን ማርከንህ፣ ብሩክ ቃልቦሬ፣ ምኞት ደበበ፣ ሱሌይማን መሀመድና ቡልቻ ሹራ ይገኙበታል፡፡ አዳማዎች ከሕጉ መውጣት በፊት የነበረ ውል አለማክበራቸው ፌዴሬሽኑ እንደማይቀበለው አሳውቋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የተናገሩት የፌዴሬሽኑ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን “በክለቦች ዝርክርክ የሆነ አሰራርና ሕግን አክብሮ አለመስራት ፌዴሬሽኑ በፊፋ የሚቀጣበት ምክንያት የለም፤ ስለዚህ ሕግ የማስከበር ኃላፊነታችንን እንወጣለን ነገሮች እየከረሩ ሲመጡ ቅጣቱ ወደ ፌዴሬሽኑ የማይዞርበት ምክንያት ስለማይኖር’ እርምጃ መውሰዳችን አይቀርም፡፡ ክለቦች በትክክለኛ መንገድ የሚጠበቅ ባቸውን እየከፈሉ መጓዝ መቻል አለባቸው” በማለት ለሀትሪክ ተናግረዋል፡፡ በክለቡ ውሣኔ ዙሪያ መረጃ ለማግኘት ወደ ፕሬዚዳንቱ አቶ ገመቹ ስልክ ብንደውልም ልናገኛቸው ባለመቻላችን ምላሹን ማወቅ አለመቻላችንን እንገለፃለን፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...