መነሻ ገጽ አዳማ ከተማ አስተያየት | ወልቂጤ ከተማ 0-2 አዳማ ከተማ
አዳማ ከተማወልቂጤ ከተማዜናዎችየአሰልጣኞች አስተያየት

አስተያየት | ወልቂጤ ከተማ 0-2 አዳማ ከተማ

አጋራ
አጋራ

 

አሰልጣኝ ደጉ ዱባሞ – የአዳማ ከተማ ምክትል አሰልጣኝ

ስለጨዋታው

” በጨዋታው ያሰብነውን ያህል ኳሱን ተቆጣጥረን መጫወት አልቻልንም። በውጤት ደረጃ ብናሸንፍም በእንቅስቃሴ ረገድ ጨዋታው ያሰብነውን አይገልጽም። ውጤቱ የእኛን እንቅስቃሴ የሚገልፅ አይደለም ::”

አስበን ወደ ሜዳ የገባነው የነበረው ኳሱን ይዘን መጫወት ነበር። በእረፍት ሰአትም የተነጋገርነው ጨዋታችን ልክ እንደልነበረ ነው ::

ታክቲካሊ ተጫዋቾቻችን ሙሉ ለሙሉ ያሰብነውን አልተገበሩልንም ማለት እንችላለን። ሁላችንም የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ አለብን ብለን ነበር የገባነው። የጨዋታው ውጤቱ ጥሩ ቢሆንም ጨዋታችን ረጃጅም ኳሶች ይበዙት ነበር።”

ተጫዋቾቼ ሰአት የመግደል ነገር በፍፁም አላሰብነውም ለግብ ጠባቂያችንም ቢሆን እንዲህ አይነት ነገሮች እንዳይደረጉ መልእክቶችን ልከናል ::

አሰልጣኝ ደግአረግ ይግዛው – ወልቂጤ ከተማ

ጨዋታው ቆንጆ ነበር በቅድሚያ አዳማዎችን እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እወዳለሁ። ተጫዋቾቻችን እንዳያችሁት በ90 ደቂቃ ውስጥ አቅማቸው የፈቀደውን አድርገዋል።

በእግርኳስ ውስጥ ያልተጠበቀው ነገር ይከሰታል። በእርግጥ በመጀመሪያው 45 ብልጫዎች ተወስደውብን ነበር፤ ከኛ የተሻለ መንቀሳቀስ ችለው ነበር :: በሁለተኛው አጋማሽ ደግሞ ክፍተቶቻችን አርመን የተሻለ ነገር ለመስራት ሞክረን ነበር። በዚህም በተደጋጋሚ ወደ ጎል መድረስ ብንችልም አጋጣሚዎችን መጠቀም አልቻልንም። እንደ ጨዋታ ግን ተጫዋቾቼ ውጤቱን ለመቀልበስ ባደረጉት ተጋድሎ እጅግ ደስተኛ ነኝ።”

የመከላከል አደረጃጀታችን ባለፉት ጨዋታዎች ጠንካራ ነበር በዛሬው ጨዋታ ላይ ግን አራቱም ቋሚ የተከላካይ ክፍል ተጫዋቾቻችን በጉዳት ያጣንበት ሁኔታ ነበር ::

ተጫዋቾቼ ባሳዩት ነገር ደስተኛ የተገኘውን ውጤት በፀጋ ነው የምንቀበለው ያለውን ውጤቱ ሙሉ ሀላፊነትን የምወስደው እኔ ነኝ ለተጫዋቾቼ ከፍ ያለ ምስጋና በዚህ አጋጣሚ የማቀርበው ::

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

ገረሱ ሸመና መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቀለ

በሊጉ ለመቆየት እየዳዱ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታዎች ረዳት አሰልጣኝ ሾመዋል። በኢትዮጵያ እግር...

ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...