መነሻ ገጽ ወላይታ ድቻ አስተያየት| ወላይታ ድቻ 3-0 ድሬዳዋ ከተማ
ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግድሬዳዋ ከተማ

አስተያየት| ወላይታ ድቻ 3-0 ድሬዳዋ ከተማ

አጋራ
አጋራ

 

ሶዶ ላይ በ12ኛው ሳምንት መርሀ ግብር ወላይታ ድቻ ድሬዳዋን ካሸነፈ በኋላ የሁለቱም ቡድን አሰልጣኞች አስተያየታቸውን ሰጥተውናል።

ከመጀመሪያው ሰከንድ ጀምረን ለማጥቃት ተጫውተን አሸንፈን ወጥተናል (ደለለኝ ደቻሳ የወላይታ ድቻ ጊዚያዊ አሰልጣኝ)

ስለጨዋታው

ጨዋታው እንዳያችሁት ነው። በታሪክ ደግሞ ድሬዳዋን ስናሸንፍ ይህ ለመጀመሪያ ግዜ ነው። ባለፈው ሳምንት እራሳችን በሰራነው ስህተት ነው ነጥብ አጥተን የተመለስነው። ቢሆንም ስህተቶቹን ለቅመን በመስራት በደጋፊያችን ፊት ጥሩ ውጤት ይዘን ለመውጣት ነው የገባነው። እንዳያቹህ ከመጀመሪያው ሰከንድ ጀምረን ለማጥቃት ተጫውተን አሸንፈን ወጥተናል።

በሁለተኛው አጋማሽ መቀዛቀዛቹ ውጤት አስጠብቆ ከመውጣት ጋር ሊያያዝ ይችላል ?

አዎ በመጀመሪያው አጋማሽ እንደተመለከታችሁት ሶስት ግቦችን አግብተናል። ሁለተኛው አጋማሽ ግን ጥንቃቄ መሰረት አድርገን ነው የገባነው። ግባችንን ዘግተን ማጥቃት ባለብን ስአት እያጠቃን ነበር። ይህም ደግሞ ተሳክቶልናል።

በ45 ደቂቃ ነው ተሸንፌ የወጣሁት ስምዖን አባይ (ድሬዳዋ ከተማ)

ስለጨዋታው

እንግዲህ እግር ኳስ ይህ ነው። በ45 ደቂቃ ነው ተሸንፌ የወጣሁት። ያማለት ደግሞ በመጀመሪያው ግማሽ የኛ ቡድን ፈፅሞ ዝግጁ አልነበረም። ከወገብ በታች እና መከላከሉ የተበታተነ ብሎም ያልተቀናጀ ነበር። እነሱም ይህን ተጠቅመው ሶስት ግቦችን በተከታታይ ሊያስቆጥሩብን ችለዋል። በመጀመሪያው ግማሽ ከነበራቸው እንቅስቃሴ ሶስት ግቦች ማስቆጠራቸው ሚያንስ ነው። በመጀመሪው ግማሽ ብልጫ ተወስዶብኝ መሸነፍ ችያለው። ተጫዋቾቼም ላይ ድካም ይታያል እንደምክንያት ባይቆጠርም።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...